Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Wedi
Member+
Posts: 7989
Joined: 29 Jan 2020, 21:44

Neamin Zeleke "ፋሽሽቱን የቀበሮ ባህታዊው አብይ አህመድን ተሎ ከስልጣን ማባረረ ግዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው!!" WEEY GUUD!!

Post by Wedi » 04 Jun 2023, 03:11

Neamin Zeleke "ፋሽሽቱን የቀበሮ ባህታዊው አብይ አህመድን ተሎ ከስልጣን ማባረረ ግዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው!!" WEEY GUUD!!
:lol: :lol:

Neamin Zeleke
June 4 2023 ·

የቀበሮ ባህታዊው አብይ አህመድ "በኢትዮጵያዊነት" እና "በመደመር" ጭንብል ሸፍኖት የነበረው ድብቅ ማንነቱ ቀስ በቀስ አየተገለጠ፣ በተለይም ባለፉት ጥቂት ወራት ደግሞ በማያሻማ ሁኔታ ሙሉ በሙሉ በመገለጡ እውነተኛ ፋሺስታዊ የእርካብና መንበር ባህሪይው ገሃድ ወጥቷል። የሚደበቅባቸውን ጭንብሎቹን ሁሉ አራግፎ ጨርሷል። አረመኔ፣ ራስ ወዳድ፣ አስመሳይ፣ ጠባብ የዘወጌ ዘረኛ ፋሽስት መሆኑ ተገልጧል። ከዚህ በኋላ ምን ሆነ፣ ማን ታረደ፣ በጥይት ተደበደ፣ ታፈነ፣ ተፈናቀለ፣ ስቆቃ ተፈጸመበት የሚሉ መርዶዎች መስማትና ማሰማት ላይ ብቻ ማተኮር ነገ ኢትዮጵያን እንደ ሃገር ማጣት ሊሆን ይችላል።

በአብይ አህመድ አገዛዝ ሳቢያ ዛሬ ሀገራችን ሁለንተናዊ ቀውስ ውስጥ ተዘፍቃለች። ከዚህ በኋላ ዋናው ትኩረት በምን በምን አይነት አደረጃጀት? ለምን አላማ? ወዴት ለመድረስ? እንዴት በውጭም በውስጥም በሚደረጉ ሁለገብ የትግል እንቅስቃሴዎች ተናበውና ተጠናክረው የአብይ/የኦህዴድ/ኦሮሚያ ብልጽግና ፋሽታዊ አገዛዝን ታግሎ ማስወገድ፥ ወይንም ማስገደድ የሚለው የሁሉም የህብረተስብ ክፍል ቀዳሚ አጀንዳ ሊሆን ይገባል።

የእብይ እህመድ የኦሮሚያ ብልጽግና ፋሽስታዊ አገዛዝ ህዝብን ንቆአል፣ በእብሪትና በትብኢት ተወጥሮአል። አይኖች ታውረዋል፣ ጆሮዎች ተደፍኖአል። የግፍ ጽዋ ሞልቶ ፈሶአል። በቅንጦት ኑሮና በSuV የሚንበሸበሹት አብዛኞቹ የአገዛዙ ሹሞችና ሚኒስትሮች ጥቅማ ጥቅሞቻቸውን ማስቀጠል እንጂ በህዝብ ላይ የሚደርሰው በደል ለመስማት፣ የህዝብን ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችል ሂሊና ተደፍኖባቸዋል። ምክነያቱ ግልጽ ነው። እብዛኞቹ የወጡበት የኋላ ታሪካቸው፣ ያለፈው የጭቆና እና የግፍ አገዛዝ የታዛዥነት፣ የአድርባይነት፣ የተላላኪነት/ የሎሌነት ታሪካቸው ከዚያ ውጭ እንዲያስቡ ፣ እንዲያደርጉም አይፈቅድላቸውም።

የኢትዮጵያ ህዝብ ከአብይ አህመድ ብልጽግና ምን አተረፈ? የሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያን ሞት ፣ ረሃብ፣ ጉስቁልና፣ ሰቆቃ፣ እልቂት፣ መፈናቀል፣ ጦርነት፡ ስደት፣ እና ልመና! የኢትዮጵያ ስፊ ህዝብ ፣ ሰፊው የኦሮሞ ህዝብም ሁለንተናዊ መብቶቹ፣ ፍትህን፣ እኩልነትን፣ የተረጋጋ ህይወትን የወዲያኛው አለም ሆነውበታል። ለሁሉም ማህበረስብና ለሁሉም ዜጎች በእኩል እይን የሚያይና የሚያገለግል ፍትሃዊ የፓለቲካ ስርአትን በእጅጉ ይናፍቃል። #JusticeForEthiopia #DefundAbiy #RerouteRemittance

:!:
Please wait, video is loading...


gearhead
Member+
Posts: 5526
Joined: 08 Jun 2014, 16:29

Re: Neamin Zeleke "ፋሽሽቱን የቀበሮ ባህታዊው አብይ አህመድን ተሎ ከስልጣን ማባረረ ግዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው!!" WEEY GUUD!!

Post by gearhead » 04 Jun 2023, 04:06

የሚያወርድ የሰቀለ እንጂ እራሱን ያለስሌት የለጠፈ አይደለም!! ነአምን አልነበረም ስለዚህ የለም!! His pretension of king maker, above the king is found wanting and he is in shock.

አለመኖሩን ሲረዳ፣ ደንብሮ የሚቸከችከው ነገር አያደናብራችሁ!!

eden
Member+
Posts: 9257
Joined: 15 Jan 2009, 14:09

Re: Neamin Zeleke "ፋሽሽቱን የቀበሮ ባህታዊው አብይ አህመድን ተሎ ከስልጣን ማባረረ ግዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው!!" WEEY GUUD!!

Post by eden » 04 Jun 2023, 09:21

looks like the author very carefully avoided attacking Berhanu Nega who serves Abiy full time. Hypocrisy! It kind of feels like the entire message was being self sabotaged from getting across. it must be agonizing to write while harboring unresolved internal conflict.
በቅንጦት ኑሮና በSuV የሚንበሸበሹት አብዛኞቹ የአገዛዙ ሹሞችና ሚኒስትሮች ጥቅማ ጥቅሞቻቸውን ማስቀጠል እንጂ በህዝብ ላይ የሚደርሰው በደል ለመስማት፣ የህዝብን ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያስችል ሂሊና ተደፍኖባቸዋል። ምክነያቱ ግልጽ ነው። እብዛኞቹ የወጡበት የኋላ ታሪካቸው፣ ያለፈው የጭቆና እና የግፍ አገዛዝ የታዛዥነት፣ የአድርባይነት፣ የተላላኪነት/ የሎሌነት ታሪካቸው ከዚያ ውጭ እንዲያስቡ ፣ እንዲያደርጉም አይፈቅድላቸውም።

Right
Member
Posts: 2808
Joined: 09 Jan 2022, 13:05

Re: Neamin Zeleke "ፋሽሽቱን የቀበሮ ባህታዊው አብይ አህመድን ተሎ ከስልጣን ማባረረ ግዜ የማይሰጠው ጉዳይ ነው!!" WEEY GUUD!!

Post by Right » 04 Jun 2023, 09:34

Neamin Z, welcome to the progressive force. Never too late. We hope Dr BERHANU N will jump the sinking ship and join the mass movement.

There will never be a place for dictatorship and ethnic federalism in the Horn of Africa.

Post Reply