Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

የእሁድ ዘፈን ምርጫ

Post by Revelations » 28 May 2023, 19:11


Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: የእሁድ ዘፈን ምርጫ

Post by Revelations » 28 May 2023, 21:53


Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: የእሁድ ዘፈን ምርጫ

Post by Revelations » 28 May 2023, 23:31


almaze
Member+
Posts: 5304
Joined: 15 Dec 2013, 03:38

Re: የእሁድ ዘፈን ምርጫ

Post by almaze » 28 May 2023, 23:43

ሰላም ለዚ ቤት!





Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: የእሁድ ዘፈን ምርጫ

Post by Revelations » 29 May 2023, 01:05

ቤት ለእንቦሳ ብለናል!

ጥሩ ምርጫ ነው:: በሞጋሳ የገቡ የሰላላ/ሰላሌ ሰዎች ይመስላሉ :: ግን እስክስታቸውን አልረሱትም!


almaze wrote:
28 May 2023, 23:43
ሰላም ለዚ ቤት!





Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: የእሁድ ዘፈን ምርጫ

Post by Revelations » 29 May 2023, 01:53

መግቢያዬ ላይ እንዳወሳሁት ጀኔራል ታደሰ ብሩ የተወለዱበት አገር ሰላሌ ኦሮሞ ወደ ቦታው ከመስፋፋቱ በፊት የአማራ አገር ነበር። በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የቱለማ የኦሮሞ ጎሳዎች ከብቶቻቸው እየነዱ ሸዋን ወረው ባለ ርስቱን ገበሮ፣ ጠለታና ገርባ በማድረግ የቦታውን ስያሜ ሰላሌ ብለው corrupt ከማድረጋቸው በፊት የቦታው ትክክለኛ መጠሪያ ሰላላ የሚል የአማርኛ ስም ነበር። ሰላላ አማርኛ ነው። ሰላላ የሚለው የአካባቢ መጠሪያ ኦሮሞ ወደ ቦታው ከመስፋፋቱ በፊት በተጻፈው የዐፄ ሱስንዮስ ዜና መዋዕል ውስጥ ተጠቅሶ ይገኛል። የዐፄ ሱንዮስ ጸሐፌ ትዕዛዝ አዛዥ ተክለ ሥላሴ ዐፄ ሱስንዮስ በአያታቸው ምድር በሸዋ ያሳለፉትን የወጣትነት ዘመን በገለጹበት የዜና መዋዕሉ ክፍል እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል፤

“ወበውእቱ ምድረ ረከቦ ዓብይ ምንዳቤ ረኅብ እስከ በልኡ ሠራዊቱ አሣእነ እግሪሆሙ። እስመ ተኃጥ አእክል ለሲሳይ በእንተ ዘኮነት ይእቲ ምድር በድወ ወዓጸ። ወእምዝ ተንሥአ እምይእቲ ምድር ወአመልአ ፍኖቶ መንገለ ግንድ በረት ። ወእምዘ የሐውር በጽሐ ምድረ ሰላላ።” [Pereira, F. M. E. (1892). Chronica de Susenyos, Rei de Ethiopia: Texto ethiopico: destinado á X sessão do congresso internacional dos Orientalistas. Imprensa nacional; Page 22 ]

ትርጉም፤

ያንጊዜም ሐንገታሞ በሚባል ስፍራ ተቀመጠ። በዚያም ስፍራ ታላቅ የርሐብ ችግር ገጠመው፤ ተከታዮቹ የእግራቸውን ጫማ እስኪበሉ ድረስ። ለምግብ የሚሆን እህል ታጥቷልና፤ቦታዋ ምድረ በዳና ደረቅ ስለሆነች። ከዚህ በኋላ፣ ከዚያች ቦታ ተነስቶ ወደ ግንደ በረት ጉዞ አደረገ። ሲሄድም ሰላላ ደረሰ።

ሐንገታሞ ደብረ ብርሀን አካባቢ የሚገኝ አገር ነው። ግንደ በረትም አሁንም ድረስ ሸዋ ውስጥ የሚገኝ ቦታ ነው። ዜና መዋዕሉ እንደሚነግረን ዐፄ ሱስንዮስ ከደብረ ብርሀን አካባቢ ተነስቶ ወደ ግንደ በረት ለመሄድ ሰላላ አድሯል። ይህ ሁሉ ታሪክ የተፈጸመው ኦሮሞ ወደ ቦታው ከመምጣቱ ከአንድ ክፍለ ዘመን በፊት ነው።

ሰላላ በአማርኛ አነጋገር ውስጥ በብዛት ጥቅም ላይ ይውላል። ጎጃም ስናድግ ልጆች ሳለን የዘመን መለዋጫ በዓልን ሲከበር በወጣቶች በሚዜሙ ጥዑመ ዜማዎች ውስጥ ሰላላ ጥቅም ላይ ይውል ነበር። በበዓሉ እለት ከሚዜሙት ጥዑመ ዜማዎች መካከል ሴት ቆነጃጅት እንዲህ እያሉ ያዜሙ ነበር፤

የቅዱስ ዮሐንስ ያልዘፈነች ቆንጆ፣
ቆማ ትቀራለች እንደ ሰፈር ጎጆ፤
እቴ አደይ አበባ ነሽ፣
ዉብ ነሽ ዉብ ነሽ፤

ልጃገረዶች ይህንን ዜማ እንግጫ እየነቀሉ ሲያሰሙ፤ ጎረምሶች ወንዶች ደግሞ የሚከተለውን እያዜሙ ወደ ልጃገረዶች ይሄዳሉ፤

እንግጫችን ደነፋ፣
ጋሻዉን ደፋ፤
እንግጫዬ ነሽ ወይ፤

ኮረዶች ይህንን ሲሰሙ እንዲህ ብለው ይመልሳሉ፤

እሰይ እሰይ፣
የቅዱስ ዮሐንስ የመስቀል የመስቀል፤
የላክልኝ ድሪ ሰላላ መላላ፣
መልሰህ ዉሰደዉ ጉዳይም አይሞላ፤

በዚህ ጊዜ ጎረምሳው ለወደዳት ልጃገረድ ማተብ ያስርላታል። ጨዋታው እንዲህ እንዲያ እያለ ይደራ ነበር. . .

Revelations
Senior Member+
Posts: 33713
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: የእሁድ ዘፈን ምርጫ

Post by Revelations » 29 May 2023, 02:03


TGAA
Member+
Posts: 5624
Joined: 07 Apr 2019, 20:34

Re: የእሁድ ዘፈን ምርጫ

Post by TGAA » 29 May 2023, 02:45

Revelations wrote:
28 May 2023, 23:31
Let us add this to your Sunday collections : ኩሪ ኩሪ ግ ድ የለም


Post Reply