ሦስት ሚሊዮን ነዋሪዎች የከፋ ድህነት ውስጥ ናቸው ተብሏል
ከአጠቃላይ የአካባቢዎቹ ነዋሪዎች አንድ ሦስተኛ የሚሆኑት መጎዳታቸው ተገልጿል
በሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች በተለይም ማዕከሉን በትግራይ ክልል አድርጎ ለሁለት ዓመታት በተካሄደውና በሌሎች የተወሰኑ አካባቢዎች በነበረው ጦርነት፣ ከ1.5 ትሪሊዮን ብር በላይ የሚገመት ጉዳትና ኪሳራ በአገር ላይ መድረሱን ገንዘብ ሚኒስቴር ይፋ አደረገ።
ግንቦት 9 ቀን 2015 ዓ.ም. የገንዘብ ሚኒስቴርን የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ያቀረቡት ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ፣ ተቋማቸው በሰሜን ኢትዮጵያ አካባቢዎች በተካሄደው ጦርነት የደረሰውን ጉዳትና የመልሶ ግንባታ ፍላጎት የተመለከተ የዳሰሳ ጥናት (Damage and Needs Assessment) በማከናወን፣ የጥናት ውጤቱን ለመንግሥት እንዳቀረበ ተናግረዋል።
በጥናት ግኝቱ መሠረትም ያጋጠመው አጠቃላይ ጉዳትና የኢኮኖሚ ኪሳራ በአጠቃላይ 28 ቢሊዮን ዶላር እንደሚሆን ሪፖርታቸው አመላክቷል። ይህም በወቅቱ የውጭ ምንዛሪ ተመን ከ1.5 ትሪሊዮን ብር በላይ ነው።
ለቋሚ ኮሚቴው ያቀረቡት ሪፖርት ላይ ከተቀመጠው መረጃ መረዳት እንደተቻለው፣ ‹‹22 ቢሊዮን ዶላር ወይም ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት (GDP) 20.4 በመቶ የሚገመት ጉዳት›› ደርሷል።
በዚሁ ምክንያት የደረሰው የኢኮኖሚ ኪሳራ ደግሞ፣ ‹‹ስድስት ቢሊዮን ዶላር ወይም ከጠቅላላ የአገር ውስጥ ምርት (GDP) 5.5 በመቶ የሚገመት የኢኮኖሚ ኪሳራ (Economic Loss)›› መድረሱን ሪፖርቱ ያመለክታል።
ግጭትና ጦርነት በነበረባቸው አካባቢዎች ከሚገኙ ጠቅላላ ነዋሪዎች ውስጥ አንድ ሦስተኛ የሚሆኑት በጦርነቱ በቀጥታ የተጎዱ መሆናቸውን፣ ከእነዚህ ውስጥ ደግሞ ሦስት ሚሊዮን የሚሆኑት የአገሪቱ ዜጎች በጦርነቱ ምክንያት የከፋ ድህነት ውስጥ መግባታቸውንም አስረድተዋል።
ሚኒስትሩ ባቀረቡት ሪፖርት የተቀመጠው የጉዳት መጠን፣ ኢትዮጵያ ባለፉት በርካታ ዓመታት ከውጭ አበዳሪዎች ለኢኮኖሚ ልማት ተበድራ ካልመለሰችው አጠቃላይ የውጭ ዕዳ ጋር እኩል መሆኑን መረዳት ይቻላል። የገንዘብ ሚኒስቴር በየሩብ ዓመቱ ይፋ በሚያደርገው የዕዳ ሁኔታ መግለጫ መሠረት፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ያለባት አጠቃላይ የውጭ ዕዳ መጠን 28 ቢሊዮን ዶላር ነው።
በጦርነቱ የደረሰውን ጉዳት ለመቀልበስና ከጦርነት በፊት ወደነበረበት ሁኔታ ለመመለስ እንዲቻል ለአምስት ዓመታት (እ.ኤ.አ. ከ2023 እስከ 2028 ድረስ) የሚቆይ የመልሶ ማቋቋምና ግንባታ አገራዊ የዕቅድ ማዕቀፍ (Ethiopia Resilient Recovery and Reconstruction Planning Framework) መዘጋጀቱን አስረድተዋል። ለዚህ ፕሮጀክቶች ማስፈጸሚያ 20 ቢሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ በዕቅድ ማዕቀፉ መመላከቱንም ገልጸዋል።
Continue reading https://www.ethiopianreporter.com/118763/
sarcasm wrote: ↑02 Nov 2022, 20:31What if Abiy agreed for peace talks when the 3 AU Envoys begged him to peacefully resolve the conflict, how many lives would have been saved. How much infrastructure, resources, military equipment would have been saved?
No dialogue with TPLF, Ethiopia PM tells AU envoys
27 Nov 2020
Abiy rules out dialogue with TPLF during meeting with three AU envoys, a day after he announced ‘final phase’ of three-week conflict.
Ethiopian Prime Minister Abiy Ahmed has again ruled out dialogue with the Tigray People’s Liberation Front (TPLF) during a meeting with three African Union special envoys.
Abiy told the envoys trying to end the deadly conflict between Ethiopian troops and forces loyal to the TPLF that he is willing to speak to representatives “operating legally” in the northern Tigray region, The Associated Press news agency reported on Friday.
The meeting occurred as people fled the regional capital, Mekelle, in fear of an imminent assault after Abiy on Thursday announced the “final phase” of the three-week offensive.
In a statement issued after the meeting, Abiy’s office said the government was committed to the “protection and security of civilians” in Tigray.
There was no immediate word from the three AU envoys: Former Liberian President Ellen Johnson Sirleaf, former Mozambique President Joaquim Chissano and former South African President Kgalema Motlanthe.
https://www.aljazeera.com/news/2020/11/ ... m-abiy-ahm
Ethiopia: Govt Rejects AU Offer to Mediate Tigray Conflict
21 NOVEMBER 2020
By Aggrey Mutambo
Ethiopia on Saturday rejected a mediation offer from the African Union, with officials in Addis Ababa falling short of calling the office of the continental body's chairperson a purveyor of false news.
Hours after South African President Cyril Ramaphosa, the current AU Chairperson, appointed three ex-presidents to mediate in the Tigray conflict, Ethiopia termed reporting on the mediation fake news.
"PM Abiy Ahmed will be meeting the chairperson's special envoys to speak with them one on one," said a statement posted on the Prime Minister's official Twitter page on Saturday.
"News circulating that the envoys will be traveling to Ethiopia to mediate between the federal government and TPLF's criminal element is fake."
Those appointed
On Friday, President Ramaphosa appointed a team of 'Distinguished States Persons' to help end the conflict that has raged for the last two weeks as Ethiopian forces battle the Tigray People's Liberation Front.
https://allafrica.com/stories/202011230097.html