Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 10186
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

«ከማውገዛችን በፊት በቅዱስ ቃሉ መሰረት እናነጋግራቸው ሐሳባቸውን እንስማ» የሚለውን የፓትርያርኩን ሓሳብ በመቃወም፤ የነ'ሰይጣን ይግዛን' ሲኖዶስ በእብሪት የብሔረሰቦች ሲኖዶስን አወገዘ

Post by sarcasm » 29 Jan 2023, 08:53

የትናንቱ የኢትዮጵያ ሲኖዶስ ስብሰባና ውሳኔ ስለምን በቅዱስ መፅሐፍና በፓትርያርኩ የውሳኔ ሓሳብ አልተመራም?

ተጻፈ በካሳ ሃይለማርያም


ብፁዕ ወቅዱስ ኣቡነ ማትያስ ቅዱስ መፅሓፍ በሚያዘው መሰረት፤ «በመጀመሪያ ለእነአባ ሳውሮስ ጥሪ እንዲደረግላችውና ስለ ጉዳዩ በሲኖዶስ ቀርበው እዲጠየቁ፤ እዲሁም እንዲጠይቁ መጀመሪያ እንስማቸው» በማለት ለጉባኤው የውሳኔ ሐሳብ አቅርበው እንደነበር ነው:: የሲኖዶሱ አባላት ግን በአብላጫ ድምፅ «አንቀበልም በአስቸካይ አውግዘን ለይተናቸው ጉባእያችንን እንጨርስ» በማለት ፓትርያርኩን እንደተቃወሙዋቸው ለማወቅ ተችሏል::
ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስጋዌዉ ወንጌለ መንግስት ለደቀመዛሙርቱ ሲያስተምራቸው፤ በማቴዎስ ወንጌል ከ18:15 ጀምሮ ሰፍሮ የሚገኝና "አባቶች" ነን የሚሉ አዘውትረው "የሚያስተምሩት"፤

«በመጀመሪያ ወንድምህ ቢበድልህ ሄደህ አንተና እርሱ ብቻህን ሆነህ ምከረው:: ቢሰማህ፣ ወንድምህን ጠቀምከው:: ባይሰማህ በሁለተኛው ጊዜ ከአንተ ጋር ሁለት ወይም ሶስት ምስክር ያዝና አነጋግረው፤ ነገር ሁሉ በሁለት ወይም በሶስት ምስክር ቃል ይፀናልና:: እነርሱንም ባይሰማቸው ግን ለቤተ ክርስቲያን ንገር፤ ቤተ ክርስቲያንንም ባይሰማ ግን፤ እንደ አሕዛብና እንደ ቀራጭ ይሁንልህ» ብሏል::
ቅዱስ አባታችን አቡነ ማትያስም በዚህ የጌታ ቃል መሰረት በቤትክርስትያኒቱና በልጆቿ በንግግር በሽምግልና ጉዳዩን ለመቋጨት ነበር ሐሳባቸውን ያቀረቡት::


ግን ሲኖዶስ ውስጥ ያለው ጉዳይ ከጌታ ቃልና ከኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖት ጋር የማይገናኝ ስለሆነ፤ በቅዱስ አባታችን ሐሳብ ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነሳ:: የኢትዮጵያ ሲኖዶስ ማለት ከ60% በላይ «ሰይጣን ቢገዛን ይሻለናል» የሚሉ የተሰገሰጉበት የፋኖ ምሽግ ነው:: በአገር ውስጥ አድባራት ብቻም ሳይሆን በመላው ዓለም የተለየ አማኝ በመምሰል በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መሽገው በሰው ልጅ ላይ ጦርነትን ዕልቂትን የሚያውጁ፤ «ደም አፍስስ ትውልድ ዘር አጥፋ» ብለው ጦርነት የሚባርኩ፤ ለሰው እልቂት ለጦርነትና ለፋኖ በገንዘብ በምክር በማቴሪያል የሚደግፉ አራጣ አበዳሪዎችና ቀራጮች ናቸው::

መሆኑም ነው «ከማውገዛችን በፊት በቅዱስ ቃሉ መሰረት እናነጋግራቸው ሐሳባቸውን እንስማ» የሚለውን የቅዱስ ፓትርያርኩን ሓሳብ አጥብቀው በመቃወም፤ በዘመነ አዲስ ኪዳን አይደለም በብሉይ ኪዳን ዘመንም ያልነበረ፤ ፍፁም ጨካኝ የፈሪና የአረመኔ ውሳኔና መግለጫ ያወጡት:: ሲኖዶስ ተከፋፈለ ማለት የመጨረሻው የፋኖ ምሽግ መፍረሱ ስለሆነ ነው!

የማርቆስ ወንጌል 16:15 ላይ ጌታ ለደቀመዛሙርቱ፤ «ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ፤ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ» ነበር ያላቸው:: ለፍጥረት ሁሉ ሲል በዓለም ላይ ባሉ ቋንቋዎች ሁሉ እንጂ በ*ማርኛ ብቻ ማለት አልነበረም፤ በወቅቱ ይህ ቋንቋ ስለመኖሩም ጥናት ያስፈልገዋል:: እና አሁን ሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች በሚያውቁት በእናት አፍ መፍቻ ቋንቋቸው ቢፀልዩ ቢገለገሉ አድባራትን ቢያስተዳድሩ ሃጢኣታቸው ምኑ ላይ ነው!

በትግራይ ሕዝብ ላይ እየተካሄደ ባለው የዘር ማጥፋት ጦርነት እሳት ሲያቀጣጥል፤ የትግራይን ሕዝብ ከህልውና እንዲጠፋ እንዲጨፈጨፍ ከታሪክ አሻራ እንዲፋቅ በመፎከር፤ የፋኖ የቀኝ ክንፍ በመሆን እንደ መርዝ የከፋ ንግግር ሲያደርግ የነበረ አሕዛብ፤ እንዴት አሁን ተገልብጦ ብቸኛ የሃይማኖቱ ተቆርቋሪ እኔ ነኝ አለ!

በፍፁም አረመኔነት የሰውን ልጅ ከእነ ህይወቱ በእሳት የሚያቃጥለው፤ ፈጣሪ በአምሳሉ የፈጠረውን የሰውን ልጅ እንደ እንሰሳ አንገት ቆርጦ አርዶ፤ የሰውን ልጅ ጭንቅላት እንጨት ላይ ሰክቶ ለትዕይንት የሚያዞረው ፋኖ፤ ከአፅናፍ እስከ አፅናፍ ይህን ያህል የተንጫጫው፤ እውነት ስለኦርቶዶክስ ሃይማኖት ተቆርቁሮ ወይስ ሲኖዶሱ የመጨረሻ የፋኖ የነፍጠኛ ምሽግ ስለሆነ!

ለነገሩ ከቅዱስ አባታችንና ጥቂቶ አባቶች በስተቀር አብዛኞቹ የዚህ ሲኖዶስ አባላት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ በጦር ወንጀል ውስጥ የተዘፈቁ ናቸው:: የእናት ቤተክርስትያን ባለቤት የፅዮን ምድርና ልጆቿ እሳት ሲዘንብባቸው፣ ካህናት ዲያቆናት መነኮሳት በመቶዎች ሺዎች ምእመናን ሲታረዱ ሲደፈሩ፣ እሳትና ላምባ ያቀበሉ እነዚህ "አባቶች ነን" ባዮች አይደሉምን! የእነዚህ አረመኔዎች፤ የዲሲው ፋኑኤል እንዲሁም የእየሩሳሌሙ ነብሰ ገዳይ ዕንባቆም ዓይነት የዘር ማጥፋት ወንጀለኞች ስብስብ ሲኖዶስ ነው፤ ኦርቶዶክስ ተደፈረች ብሎ ተሯሩጦ ይህንን ዓይነት በአንድ ጀምበር በአጭር ሰዓት ውስጥ ጨካኝ የኢአባትነት ውሳኔ ያስተላለፈው::

እውነት እዝነ ልቦና ያለው ሰው ይፍረድ፤ በትናንቱ ስብሰባ ለማውገዝ ዋና አቀንቃኝ የነበረው የእየሩሳሌሙ ዕንባቆም እኮ፤ በእየሩሳሌም መነኮሳትን ተጋሩ ስለሆኑ ብቻ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ ከአፀደ ቤተ ክርስቲያን አባርሮ ፓስፖርታቸውን ቀምቶ፤ ከቤተክርስትያን ገብተው የመድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ቅዱስ ስጋውና ክቡር ደሙን እንዳይቀበሉ የከለከለ፤ ከቅፅረ ቤተክርስታኒቱ እንዳይገቡ እንዳይሳለሙ ያገደ አረመኔ ግለሰብ ነው:: እንግዲህ እነዚህ ናቸው "አባቶች" የሚባሉት አማኞችና አውጋዦች "ኦርቶዶክስን የሚታደጓት"!

ኦርቶዶክስን ለማዳን ከልብ ለሚተጉ ሁሉ ስለእነዚህ ኢአባታውያን ቀራጮች ጎጠኛነት ለማወቅ ብዙ ፋይል ማገላበጥ አያስፈልግም:: ከዚሁ ፅሑፍ ጋር የተያያዘውን አንድ ሰነድ ብቻ ከትናንትናው የተጣደፈ ውሳኔያቸው አኳያ በጥሞና ተመልከቱት:: በቅርቡ በ2012 ዓ.ም ነው በዚሁ በቅዱስ ኣባታችን በአባ ማትያስ ዘመን፤ በአማራ ክልል በጎጃም እንደአሁኑ ተመሳሳይ የሆነ እራስን የጵጵስና ማዕረግ መስጠት ተከስቶ ነበር:: እናማ ሰነዱ ላይ በግልፅ እንደሚታየው በወቅቱ ይህንን የፈፀሙት ለአብዛኞቹ የሲኖዶሱ አባላት የጎጣቸው ሰው ስለሆኑ፤ እንዳይወገዙ በከፍተኛ ርብርብ ሲከላከሉ፤ ብዙ ርቀት በሽምግልና ተኪዶበት፤ ከበቂ በላይ ጊዜ ተሰጥቶት ነው እልባት ላይ የተደረሰው!

እናማ አሁን ኦሮሞውና ሌላው ኦርቶዶክሳዊ አማኝ ሃይማኖታዊ የአገልግሎት መብቴን በማለቱ ምነው የጌታ ቃልንና የቅዱስ አባታችንን ልመና ረግጣችሁ፤ በአንድ ጀምበር ይህን ዓይነት ኢአባታዊ ውግዘት አዘነባችሁ!

ዋናው ጉዳይ ግን አብይ አሕመድና ሎሌዎቹ ስራቸውን እየሰሩ ነው:: በውስጥ ስብሰባዎቹ ላይ ለእነ ተመስገን ጥሩነህ ቡድን ደጋግሞ የሚሰጣቸው መመሪያ «እራሳችን አደራጅተን እራሳችን የምንቆጣጠረውና የምንመራው ስጋት መፍጠር፤ በመጨረሻም በቁጥጥራችን ስር አድርገን እንደምናስቆመው እርግጠኛ በመሆን፤ የሕዝቡን ስጋት ለፖለቲካ ግብዓት በማዋል፤ አገሪቱን ወደ ብልፅግና ለማሻገር በምናደርገው ፈታኝ ጉዞ፤ ለመንግስታችን ህልውና አንድ ዋስትና ነው:: ሕዝቡ ትናንት ከዛሬ ይሻላል፤ ነገ ደግሞ ከዛሬ እንዳይብስ የሚል ውጥረት ውስጥ መቆየቱ ትኩረቱን ከመንግስት ላይ ያነሳና በስጋቶች ላይ ይጠመዳል... ከዚያ መንግስት ስጋት አጥፊ፤ በቋፍ ላይ ለደረሰ ጉዳይ በነፍስ ደራሽ ይሆናል» ይላል አብይ አሕመድ!

ስለዚህ አሁን እሳቱን በኦርቶዶክስ ውስጥ በደህንነቱ ደጀኔ መሪነት አቀጣጥሎ እየመራው ነው፤ ትንሽ ቆይቶ ደግሞ "ኦርቶዶክስን ያስታረቀ ነብይ" ሆኖ ይመጣል!


በአማራ ክልል በጎጃም እንደአሁኑ ተመሳሳይ የሆነ እራስን የጵጵስና ማዕረግ መስጠት ተከስቶ ነበር:: እናማ ሰነዱ ላይ በግልፅ እንደሚታየው በወቅቱ ይህንን የፈፀሙት ለአብዛኞቹ የሲኖዶሱ አባላት የጎጣቸው ሰው ስለሆኑ፤ እንዳይወገዙ በከፍተኛ ርብርብ ሲከላከሉ፤ ብዙ ርቀት በሽምግልና ተኪዶበት፤ ከበቂ በላይ ጊዜ ተሰጥቶት ነው እልባት ላይ የተደረሰው



Please wait, video is loading...


Post Reply