Page 1 of 1

Gambellan responds to Berhanu Nega

Posted: 28 Jan 2023, 13:28
by Noble Amhara

Re: Gambellan responds to Berhanu Nega

Posted: 28 Jan 2023, 17:45
by Horus
Noble Amara,
I am sure you can think better than this. Berhanu Nega told us exactly what Jekap Omod tells us. There is no education system in Ethiopia. 40% of the entire Ethiopian high schools could not pass a single student on the Matrik exam. out of 1 million tested only 30k got scores higher than 50% . Ditto. There is no education in Ethiopia. Berhanu Nega came to MoE 1 year ago, not 12 years ago, not 30 years ago. Please leave him alone. If you don't want to him be there name a person who is better than him for Job! It is now a historic fact that by smashing the ugly ኩረጃ system, he has exposed to the world the 30 years long crime of TPLF, OPDO, etc. That alone is a remarkable success so far on his part. Disempowered አበሻ አህያውን ፈርቶ ዳውላውን ይባላል!!

Re: Gambellan responds to Berhanu Nega

Posted: 28 Jan 2023, 17:54
by Noble Amhara
This reveals high lack of knowledge in rural areas in ethiopia... Unless the Gov does not invest into these schools and gives them the right curriculum teaching how will they progress in life?

This may backfire so Berhanu should get to work change something to cause at least 10% or 30% passing

Re: Gambellan responds to Berhanu Nega

Posted: 28 Jan 2023, 18:28
by Sam Ebalalehu
What do people who criticize Berhanu want him to do ? ዩኒቨርስቲዎችን ብቃት በሌላቸው የ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች ይሙላው።
ዩኒቨርስቲ ከ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በጣም የተለየ ነው። የ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች በአብዛኛው እራሳቸውን ነው የሚያስተምሩት። ፕሮፌሰሮች በአብዛኛው መመሪያ ነው የሚሰጡት። የተማሪዎች የ ግል ጥረት ነው ወሳኝ። ዩኒቨርስቲ በበለፀጉት አገርም እንኳ ሁሉም ዘው የሚልበት መናፈሻ አይደለም። የኢትዮጵያን ልዩ ያደረገው መንግስት ለትምህርት ውድቀት ዋና ተጠያቂ መሆኑ ብቻ ነው። የ መንግስት ደሞዝ ሳይጠይቅ ፣ የመንግሥት መኪና ሳይሻ የኢትዮጵያን የወደቀ ትምህርት ለማሻሻል የ በኩሌን አደርጋለሁ ብሎ ለሚጥር ሰው ድጋፍ እንጂ ሀሜት አይገባውም።

Re: Gambellan responds to Berhanu Nega

Posted: 28 Jan 2023, 18:39
by Noble Amhara
.. Unless reforms are not implemented into modernizing education then How can we expect even 4% to pass next year..

Re: Gambellan responds to Berhanu Nega

Posted: 28 Jan 2023, 22:53
by Horus
ኖብለ አማራ፣
የK-12 ትምህርት ፖሊሲ የሚቀረጸውና የሚመራው በጎሳ ክልሎች እስከ ሆነ ድረስ የኢትዮጵያ ትምሀር ስርዓት 100% አይለወጥም የሚለው ትክክለኛ አባባል ነው። ለምሳሌ በዚህ ሳምንት አቢይ ከምሁራን (መምህራን) ጋር ሲወያይ ታዳሚው ሁሉ ይል የነበረው ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ ሁለተኛ ደረጃ ሆነዋል ነው ያሉት ። ልብ በሉ ይህ ዝም ብሎ የቅኔ አነጋገር ሳይሆን ፋክት ነው ። ለምን በሉ?

አሁን በየኮሌጁ ያሉት ብዙ ሺዎችን እንኳን ብንተው ትላንት ት/ሚ የወሰነውን ውሳኔ እንመልከት ። የኢትዮጵያ ኮሌጆች በየአመቱ 130 ሺ ፍሬሽሜን የመቀበል ችሎታ (ወምበሮች) አላቸው ። ከዚህ በፊት 130 ሺ ሁለተኛ ደረጃ ፈተና ማለፍ የማይችል በኩረጃ ፍሬሽማን ይሆን ነበር ። ማለትም ኮሌጆች በስም ያልተጠቀሱ ሃይ እስኩል ነበሩ ። ዛሬ ት/ሚ ያለውን ስሙ ።

30 ሺ ፈተና ያለፉ አንደኛ አመት ኮሌጅ ትምህርት ይጀምራሉ ። 100 ሺ ፈተና የወደቁት የራሳቸው ሃይ እስኩል ውስጥ 12ኛን ከመድገም በየኮሌጁ ተኝተው ግን የሃይ እስኩል ትምህርቶችን በመድገም ተፈትነው ካለፉ በሚቀጥለው አመት ፍሬሽማን ይሆናሉ ። ስለዚህ በፋክት ደረጃ ኮሌጆች ሃይ እስኩል ሆነዋል ናቸው ። ልዩነቱ ቦታና ስማቸው እንጂ ትምህርትና እውቀቱ ሁለተኛ ደረጃ ማለት ነው ።

ስለዚህ የዚህ አመት ፈተና የነገረን ትልቅ ትልቅ እውነት ምንድን ነው? ዛሬ በመላ ኢትዮጵያ የኮሌጅና ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ከሚባሉት ሁሉ ማናልባት 10% እስከ 20% ቢሆኑ እንጂ 80% የሃይ እስኩል ደረጃ እውቀት ውስጥ ያሉ ናቸው ። ይህን ስል ከ1ኛ እስከ 5ኛ አመት ያሉትን የኮሌጅ ተማሪዎችን ደምሬ ነው ።

ኖብል አማራ ያነሳሃው ጥያቄ መልስ ያለው እዚህ ላይ ነው ። የኢትዮጵያ ትምህርት በሻሻል የሚጀምረው ቢያንስ ከአምስት አመት በኋላ ነው ። ይህም ማለት አሁን ያሉት በሙሉ አወቁም አላወቁ ተመርቀው ከይኒቨርሲቲዎች ይጸዳሉ በ5 አመት ውስጥ። ከሚቀጥለው አመት ጀምሮ ፈተና ያላለፈ አንድ ተማሪ ዩኒቨርሲቲ አይገባም ። ይህም ማለት ለምሳሌ በኔ ግምት በ2024 ከ50 ሺ ወይም 60 ሺ በላይ ፍሬሽማን የሚሆኑ አይመስለኝም ።

አሁን ይህ ሁሉ ክፍልና መቀመጫ ዴስኮች እና የኮሌጅ ተብዬ አስተማሪዎች ምን ይሆናሉ ? የሚለው ትልቅ ትልቅ ጥያቄ ነው ። በዚህም ምክንያት የጎሳ የክልል ፖለቲከኞች የትምህርቱን ሪፎርም፣ የብርህኑን ሃሳብ ጥለው ወይም እሱንም አንስተውት ወደ ድሮ የኩረጃ ሲስተም ሊመለሱ ይችላሉ ። ነገር ግ ን አሁን በርሃኑ ነጋ የጀመረውን ማጽዳት መንግስት ከደገፈው በ5 አመት ውስጥ በቁጥር ጥቂት የሆኑ እውነተኛ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችና እውነተኛ ኮሌጆች ይኖሩናል ።

ዛሬ ላይ ግን አለ ምንም ጥርጥር ዩኒቨርሲቲዎች ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ናቸው ። ምናልባት ከ20% ተማሪና አስተማሪዎች በስተቀር! ይህ ሃቅ ነው! ሌላ ቦታ እንዳልኩት ዛሬ የሃይ እስኩል አስተማሪዎች ለማትሪክ ፈተና ቢቀመጡ 90% ይወድቃሉ ። የዩኒቨርሲቲ አስተማሪዎች የሚያስተምሩትን ሳብጀክት ተፈትነው 83% ወድቀዋል ። ማለትም የዩኒቨርሲቲ አስተማሪዎች ሁሉ መለወጥ ወይም እንደ ገና መማር አለባቸው ።

ልብ እንበል በዛሬ ቀን ኢትዮጵያ 31 ሚሊዮን ተማሪዎች አሏት ። ይህን ያክል የገዘፈ 25% ያገሪቱ ሕዝብ ነው እንዲህ ወድቆ ያለው ። ይህቺ አገር ከዚህ በላይ ችግር የለባትም ። እጅግ እጅግ ያሳዝናል ፣ ታሳፍራል ።