ዛሬ ስብሰባ በመኖሩ ባለስልጣን ነን በሚሉ ባለመኪኖች መንገዱ ተጨናንቆ ነበር። እነዚህ ምንም እርባና የሌላቸው ባለስልጣናት ምናለ ባያውኩን? ያ ሁሉ መኪናስ ከየት መጣ?
ባልስልጣን የሚባል ሁሉ የመንግስት መኪናን መጠቀም አቁሞ በእግሩ መሄድ ወይም የህዝብ ትራንስፖርት መጠቀም አለበት።
ሌላው ገራሚ ነገር፣ አገሪቱ ለባለስልጣናት የምትከፍለው ለማመን የሚከብድ ደሞዝ ነው።
ከወጣው መረጃ ፕሬዝዳንቷ ወደ 54 ሺ ብር ሲያገኙ አብይ ደሞ 25 ሺ ብር ነውና የሌሎችን ደሞዝ ከዚህ የተለየ አይደለም። ግን ምን ስላደረጉ ነው ይህ ወጪ?
ህዝቡ የሚያገኘው ደሞዝ የሚሰቀጥጥ ነው። እኔ ያየሁት ደሞዝ አብዛኛው ከ 2000 ብር እስከ 4000 ብር ያለ ነው ምናልባት የደሞዛቸውን ሊስት ወደ ፊት አወጣዋለሁ።
ሁለት አማራጭ አለ፣ የህዝቡን ደሞዝ ከፍ ማረግ ወይም የባለሳጣናቱን ደሞዝ ከህዝቡ ደሞዝ ጋር ማስተካከል።
-
- Member
- Posts: 4207
- Joined: 27 Sep 2017, 21:56