ግጭቶቹና ጥቃቶቹ የሚከሰቱባቸው አካባቢዎች ስፋት ከጊዜ ወደ ጊዜ መጨመር እንዲሁም ያስከተሉት የሰብአዊ መብቶች ቀውስ ደረጃ አስከፊነት አንዱ አመላካች ነጥብ ነው። ይህ መግለጫ ይፋ እስከተደረገበት ጊዜ ድረስ በኮሚሽኑ ክትትል ከዚህ ቀደም ግጭት የተከሰተባቸው ወይም እየተከሰተባቸው ያሉ ተብለው የተመዘገቡ አካባቢዎች
- [1] በምዕራብ ወለጋ ዞን ውስጥ ጊምቢ ወረዳ ቶሌ ቀበሌ፣ መነ ሲቡ ወረዳ (ነጆ መንዲ ከተማ)፣ ለታ ሲቡ፣ ቦጂ ድርመጂ (ቢላ ከተማ)፣ ነጆ ከተማ፣ ቆንዳላ ወረዳ፣ ቤጊ ወረዳ፣ ቅልጡ ካራ ወረዳ፤
- [2] በምሥራቅ ወለጋ ዞን ውስጥ ዴጋ ወረዳ፣ ሳሲጋ ወረዳ፣ ጊዳ አያና ወረዳ፣ ኪረሙ ወረዳ፣ ጉትን ወረዳ፣ ሊሙ ወረዳ፣ ጅማ አርጆ፤
- [3] በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን ውስጥ ጃርደጋ ጃርቴ ወረዳ (አሊቦ፣ ጃርደጋ እና ጃርቴ ከተሞች)፣ አሙሩ ወረዳ (አሙሩ ከተማ፣ አገምሳ ከተማ እና ከ10 በላይ ቀበሌዎች)፣ ሆሮ ቡልቅ ወረዳ፣ ጉዱሩ ወረዳ፤
- [4] በቄለም ወለጋ ዞን ውስጥ ሀዋ ገላን ወረዳ (መንደር 20 እና 21)፤
- [5] በምዕራብ ሸዋ ዞን ውስጥ ሜታ ወልቂጤ ወረዳ፣ አደዓ በርጋ ወረዳ፣ ጮቢ ወረዳ፣ ጀልዱ ወረዳ፣ አቡና ግንደበረት ወረዳ፣ ግንደበረት ወረዳ፣
- [6] በምሥራቅ ሸዋ ዞን ውስጥ ቦሰት ወረዳ፣ ዱግዳ ወረዳ፣ ፈንታሌ ወረዳ፤
- [7] በአርሲ ዞን ውስጥ ጀጁ ወረዳ፣ መርቲ ወረዳ፤
- [8] በሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ ኩዩ ወረዳ ወረጃርሶ ወረዳ፣ ደራ ወረዳ፤
- [9] በኢሉ አባ ቦር ዞን ውስጥ ደርሙ ወረዳ፣ አሊጌ ሰቺ ወረዳ፤
- [10] በቡኖ በደሌ ዞን ውስጥ ጨዋቃ ወረዳ፣ ዳቦ ሃና ወረዳ፣ መኮ ወረዳ፣ ዴጋ ወረዳን ያጠቃልላሉ።
በእነዚህ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች በአይነታቸውና በቁጥራቸው የመጨመር ወይም የመወሳሰብ አዝማምያ ማሳየታቸው እንዲሁም በተለያዩ ወቅቶች የተለያዩ ቡድኖች ሙሉ ቀበሌዎችን ወይም ወረዳዎችን ጭምር ተቆጣጥረው የቆዩ መሆናቸው የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶቹን ከማባባሱም ባሻገር ተመጣጣኝና የተጎዱ ሰዎችን ብዛትና አካባቢዎችንም የሚመጥን ምርመራ ማድረግ አልተቻለም፡፡ ይህ ደግሞ የደረሰውን ጥሰት በተገቢው የሕግና የሰብአዊ መብቶች መርሆችና ድንጋጌዎች መሰረት ለመመደብ አስቸጋሪ አድርጎታል፡፡