Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 10186
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተበተኑ። ከእናታቸው ቤት ይዘው የመጡትን ሻንጣ አንጠልጥለው ወደ ደሴ በእግር እየተጓዙ ነው - ዶይቼ ቬለ

Post by sarcasm » 28 Aug 2022, 19:28

የወልድያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከቅጥር ግቢው ለቀው መውጣታቸውን የዐይን እማኞች ለዶይቼ ቬለ ተናገሩ። አንድ የዩኒቨርሲቲው ተማሪ ከቅጥር ግቢው ለቆ መውጣቱን ለዶይቼ ቬለ አረጋግጧል። ዶይቼ ቬለ በጉዳዩ ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ ለመጠየቅ ወደ ወልድያ ዩኒቨርሲቲ ባለሥልጣናት በተደጋጋሚ ስልክ ቢደውልም መልስ ማግኘት አልቻለም። የከተማው ነዋሪዎች ግን ተማሪዎቹ "ከእናታቸው ቤት ይዘው የመጡትን ሻንጣ አንጠልጥለው" ሲጓዙ መመልከታቸውን ይናገራሉ። አንድ የወልድያ ከተማ ነዋሪ "አቅም ያለው በእግሩ እየሔደ ነው። አቅም የሌለው ደግሞ ጥላ እየፈለገ ቁጭ ብሎ ሲያዝን፣ ሲያለቅስ ሲተክዝ ነው የምታያቸው" ሲሉ ተናግረዋል።

"ለቁርስ ይሁን ለምን ይሁን ይዘውት የወጡትን ዳቦ ቁጭ ቁጭ ላለው ወታደር ሲያበሉ፤ ውኃ ሲያጠጡ እኔ በዐይኔ አይቻለሁ" የሚሉት የወልድያ ነዋሪ የተማሪዎቹን ሁኔታ "በጣም አንጀት የሚሰብር" ሲሉ ገልጸውታል። ሌላ የወልድያ ከተማ ነዋሪ በበኩላቸው "ትራንስፖርት የለም። ተማሪዎቹ በእግራቸው ለቀው ወጥተዋል" ሲሉ የተመለከቱትን ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።

በወልድያ ከተማም ይሁን በዙሪያዋ በሚገኙ አካባቢዎች የጦር መሳሪያ የተኩስ ልውውጥ ድምጽ እንደማይሰማ የዐይን እማኞች ይናገራሉ። ይሁንና የኢትዮጵያ መንግሥት እና የትግራይ ኃይሎች የሚያደርጉት ውጊያ ነሐሴ 18 ቀን 2014 እንደገና አገርሽቶ ወደ ቆቦ ሲደርስ በወልድያ ነዋሪዎች ዘንድ ሥጋት መፈጠሩን አምስት የዐይን እማኞች ገልጸዋል።

Please wait, video is loading...


Post Reply