Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Assegid S.
Member
Posts: 936
Joined: 11 Aug 2013, 07:11
Contact:

ውለታ-ቢስ!

Post by Assegid S. » 04 Aug 2022, 10:39

የኢትዮዽያን ታሪክ ባነበብኩበት መፅሐፍቶች ውስጥም ሆነ ባዳመጥኳቸው የሀገር መሪ ንግግሮች፣ በአፍላነታቸው ብቻ ሳይሆን በገፋ ዕድሜያቸው ጭምር ለሀገርና ለወገን መስዋዕት ለመሆን ፍቃደኛ የሆኑ ሚሊሽያዎችን ያዋረደና የተሳደበ መሪ ከባለጊዜው ጠቅላይ ሚንስትር ውጪ አልሰማሁም! አላየሁም! ጎበዝ … ለካ ውለታ-ቢስ መሆን ውለታ ለዋለው ብቻ ሳይሆን ውለታ ሲዋልና ውለታ ሲከዳ ዕድሜ ሰጥቶት ለተመለከተውም ሰው እንዲህ ይዘገንናል? በጥቂቱ (ለቤት) ያልታመነ ለትልቁ (ለሀገር) … ነው ነገሩ።

ጠቅላይ ሚንስትሩ ለኣማራ እንደ ግለሰብ ሳይሆን እንደ ማህበረሰብ ያላቸውን ከፍተኛ ጥላቻ ጠፍተው በተከሱቱበት ዕለትም ደግመውታል። ትላንት መንግስታቸው ግራ ቀኙ ሲጠፋው … “ተነሱ ህዝባዊ ጦርነትን በህዝብ ነው የምንመክተው! ህፃን አዋቂ ሳትል … ጠመንጃ - ሳንጃ፣ ዱላ - ቢላዋ ሳትመርጥ ያለህን ይዘህ ዝመት!” ብለው እንዳላስቀሰቀሱት፤ ዛሬ ላይ የ 70 አመቱን ሚልሽያ ሳይቀር “ለሀገር ዕድገት ጠንቅ ነው” ሲሉ ዘልፈውታል።



ከኣንድ ወር በፊት … “የሚበጀን መንግስት ቢለዋወጥ እንኳ በቋሚነት ሊያገለግሉ የሚችሉ የመንግስት ተቋማትን መገንባት ነው” ብለው በመከሩበት መድረክ … "እናንተ ምን አግብቶአቹህ ነው ስለ ህወሃት አሸባሪነት የምታወሩት? ህወሃትን አሻባሪ ያለው አምና የነበረው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንጂ እናነተ አይደላችሁምና አያገባች ሁም!” በማለት … የትላንቱ ለዛሬው መሠረት አይሆንም ብለው ሲሞግቱ የሚደመጡት ጠቅላይ ሚንስትር ጊዚያዊና artificial እንጂ ኣንድም ዘላቂ ባህርይ እንደሌላቸው ጠንቅቄ አውቃለሁ።

የሚያስገርመኝ ግን በኣማራው ለኣማራው ተወክለናል ብለው ኣማራው እንደማህበረሰብ በጠቅላይ ሚንስትሩ ሲሰደብና ሲዘለፍ አፋቸውን ከፍተው የሚስቁት ናቸው። ከጥቂት ሳምንታት በፊት ጠቅላይ ሚንስትሩ “የምዕራብ ጎጃም ገበሬ በበረዶና ዶፍ ዝናብ ተመቷል፥ ይህን ሰምተዋል?” ብለው በተከበሩት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ ክርስቲያን ታደለ ላይ ሲዘብቱ፥ ሰብሉ ለወደመበት ገበሬ ከማዘን ይልቅ የጠቅላይ ሚንስትሩን ፌዝ ለማድመቅ ከፊት ተቀምጠው ይስቁ የነበሩት አቶ ደመቀ መኮንንና የብአዴን ተወካዮች ነበሩ። ዛሬ ደግሞ … ኣማራው እንደ ክልል ተጠቅሶ ከህፃን እስከ አዋቂው ሲዘለፍ የጠቅላይ ሚንስትሩን ስድብ በፈገግታ የሚያደምቁት ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ ናቸው። በእውነት … ህወሃትንም ሆነ የዚህን መንግስት ችሎታ ማድነቅ ካለብኝ፦ እነዚህን የመሳሰሉ ኣሳማዎች ከየትና ከምን ውስጥ ቆፍረው እያወጡ የማህበረሰቡ ተወካይ፣ የክልሉ ፕሬዚደንት አድርገው እንደሾሙዋቸውና እንደሚሾምዋቸው ነው።

Ethoash
Senior Member+
Posts: 26144
Joined: 20 Apr 2013, 20:24

Re: ውለታ-ቢስ!

Post by Ethoash » 04 Aug 2022, 11:14

all respect to you my dear friend and my Eritrean brother ato Assegid S.
what do u want the good doctor to do? u want him to keep the war going or end the war and start public work revoultion ? what do u really want my dear, i am dying to know what make u so mad about the good doctor for looking for exist plane ..

if u believe in war the good doctor will not stop u, u can start war with TDF , the only thing the good doctor said was i am not going to involved in new war ..if Eritrea or Amhara want to start war with TDF then let the road be rolled with red carpet for u.

Assegid S.
Member
Posts: 936
Joined: 11 Aug 2013, 07:11
Contact:

Re: ውለታ-ቢስ!

Post by Assegid S. » 05 Aug 2022, 08:56

አሁን የኣዲስ አበባ ህዝብ ለተፈላጊው እርምጃ መሠረታዊውን ደረጃ አልፎአል። ATTITUDINAL and BEHAVIORAL CHANGE አምጥቷል። አልገመገምም ባለው እድሪስ ላይ ያለውን ተቃውሞ ከኣዳራሹ ወደ አደባባዩ የሚወስድበት ቀን ናፍቆኛል።



ውለታ-ቢስ፣ አስመሳይና ዘረኛ ሆነህ ሺህ ጊዜ ብትጣፍጥ ማስቲካ እንጂ ማር አትሆንም፤ ህዝብ አኝኮ ይተፋሃል እንጂ አላምጦ አይውጥህም! ይሰማል @እድሪስ?

Post Reply