Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 10186
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

Ethiopian negotiating team is lead & dominated by elected MPs representing Amhara Region - BBC Amharic

Post by sarcasm » 28 Jun 2022, 07:38

የኢትዮጵያ መንግሥትን ወክለው ስለሚደራደሩት ግለሰቦች ምን እናውቃለን?



አስራ ዘጠኝ ወራትን ያስቆጠረውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነትን በሰላም ለመቋጨት መንግሥት ከትግራይ አመራሮች ጋር የሰላም ድርድር ለማድረግ ወስኖ ቡድን ሰይሟል።

ይህ ተደራዳሪ ቡድን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ደመቀ መኮንን የሚመራ ሲሆን ሰባት አባላትን ያካተተ መሆኑን መንግሥት አሳውቋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከሁለት ሳምንት በፊት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደተናገሩት የሰላም ጉዳይን የሚመለከት ኮሚቴ ተዋቅሮ አስፈላጊውን ሥራ እያካናወነ መሆኑን ገልጸው ነበር።

ገዢው የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴ ተከታታይ ስብሰባዎችን ባለፈው ሳምንት ካካሄደ በኋላ ይፋ እንዳደረገው መንግሥት ጦርነቱ ሰላማዊ መፍትሔ እንዲያገኝ መወሰኑን አሳውቋል።

የተደራዳሪ ቡድኑ አባልና የአገሪቱ የፍትሕ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ እንደተናገሩት፣ ፓርቲው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት ለሚያበቃበት ድርድር መመሪያዎችን አዘጋጅቶ የቡድኑን አባላት ሰይሟል።

ከትግራይ አመራሮች ጋር የሚደረገው ድርድር ሂደትም በአፍሪካ ኅብረት የሚመራ እንደሚሆን አቋሙን ይፋ አድርጓል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ለድርድሩ ሰባት አባላት ያሉት ቡድን ያሳወቀ ሲሆን፣ እነዚህ ተደራዳሪዎች እነ ማን ናቸው?

1ኛ. አቶ ደመቀ መኮንን
አቶ ደመቀ መኮንን የብልጽግና ፓርቲ አመራር አባል ሲሆኑ በአማራ ክልል እንዲሁም በፌደራል መንግሥቱ ውስጥ በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ላይ ቆይተዋል።

አቶ ደመቀ በአማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳደር እና በተለያዩ ከፍተኛ ኃላፊነቶች ላይ የሰሩ ሲሆን፣ ከዚያም በኋላ ለረጅም ዓመታት ወዳገለገሉበት የምክትል ጠቅላይ ሚኒስተርነት ሥልጣን ከመምጣታቸው በፊት ለተወሰነ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትር ሆነው አገልግለዋል።

አቶ ደመቀ የገዢው ብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት ሲሆኑ በአገሪቱ የሥልጣን እርከን ላይ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ቀጥለው ሁለተኛው ከፍተኛ መሪ ናቸው። አቶ ደመቀ በአሁኑ ወቅት በመንግሥት ውስጥ ቁልፍ የሆኑትን የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርነትና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነትን ሥልጣን አጣምረው ይዘዋል።

Continue reading https://www.bbc.com/amharic/articles/cv267p3n1vyo

Noble Amhara
Senior Member
Posts: 11626
Joined: 02 Feb 2020, 13:00
Location: Abysinnia Highlands

Re: Ethiopian negotiating team is lead & dominated by elected MPs representing Amhara Region - BBC Amharic

Post by Noble Amhara » 28 Jun 2022, 07:45

Most of them are not amhara

Post Reply