በአፋር ማቆያ ውስጥ ያሉ የትግራይ ተወላጆች ሁኔታ አሳሳቢ መሆኑ ተነገረ
በኅዳር ወር በሺዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች የትግራይ እና የአፋር የድንበር ከተማ ከሆነችው አብአላ ታፍሰው ወደ ሰመራ መወሰዳቸውን ቢቢሲ ያነጋገራቸው ግለሰቦች ያስረዳሉ።
ሮይተርስ በበኩሉ እነዚህ የትግራይ ተወላጆች ከአብአላ ከተወሰዱ በኋላ ሰመራ አቅራብያ በሚገኘው ሶሎዳ ኮሌጅ ግቢ ውስጥ መቀመጣቸውን ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከሆነ በኮሌጁ ውስጥ ቁጥራቸው ከ7000 እስከ 12000 የሚሆኑ ግለሰቦች ይገኛሉ።
ዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል በበኩሉ ባለፈው ወር በሰመራ ለሚገኙ 9000 ተፈናቃዮች ድጋፍ ማድረጉን በመግለጽ በይፋዊ የትዊተር ገፁ ላይ አስፍሯል።
ቢቢሲ ከሶሎዳ የተፈናቃዮች ማቆያ የወጣ የትግራይ ተወላጅን አነጋግሮ፣ አንዳንድ የእርዳታ ድርጅቶች 15 ኪሎ ስንዴ እና ብርድ ልብስ ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጿል።
ሮይተርስም ሁለት ተፈናቃዮች እርዳታውን መቀበላቸውን እንዳረጋገጡለት ዘግቧል።
በትግራይ እና በአፋር ድንበር ላይ በምትገኘው አብአላ ለመጀመርያ ጊዜ ውጊያ የተደረገው ታኅሣሥ 09/2014 ዓ.ም ነበር።
በከተማዋ የሚኖሩ ሰዎች አብአላን ሸኸት በማለትም ይጠሯታል።
ታኅሣሥ 09 በትግራይ ኃይሎች እና በአፋር የፀጥታ አካላት መካከል ውጊያ መካሄዱን ተከትሎ በከተማዋ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆችን ‘ደህንታችሁ ወደ ሚጠበቅበት ስፍራ እንወስዳችሏለን’ በሚል ወደ ሊላ ቦታ መወሰዳቸውን አብዋሎም ሲሳይ* ለቢቢሲ ተናግሯል።
Continue reading https://www.bbc.com/amharic/articles/c3gr31k3re5o
-
- Senior Member
- Posts: 10186
- Joined: 23 Feb 2013, 20:08
-
- Member
- Posts: 2823
- Joined: 09 Jan 2022, 13:05