Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 30911
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

ሱሊማን አብደላ፤ የአቢይ አህመድ መንግስት ከውድቀት ለመዳን ማድረግ ያለበት 4 ነገሮች

Post by Horus » 12 May 2022, 00:00

አንድ፣ ብሄራዊ ምክክር
አለ የሚባለው ብሄራዊ ምክክር ምን እንደ ሆነ በግልጽ ለህዝብ ማሳወቅ ብቻ ሳይሆን አሁን ለዚህ ሁሉ ቀውስና መከራ ምንጭ የሆነውን የዘረርና የጎሳ ጨረባ ተስካር በመሰረቱ የሚለውጥ ሃሳብና እቅድ ለህዝብ በማቅረብ ህዝባዊ አመኔታና ድጋፍ ለማግኘት አስቸኳይ መራርና ቆራጥ ፕላን ላገሪቱ ማቅረብ አለበት ።

ሁለት፣ የኑሮ ውድነት
በቁጥር አንድ የተጠቀሰ ችግር መፍታት ከቻለ መንግስት የኑሮ ውድነቱ ላይ የህዝብ ትብብር በመጠየቅ አዳዲስ የኗኗር ስልቶችን ህዝቡ እንዲጠቀም ለማድረግ መሞከር።

ሶስት፣ የጦርነት ዝግጅት
ይህ አዲስ የጦርነት ዝግጅት ሊሳካና በትግሬ ወያኔ ላይ ብሄራዊ አንድነት መንግስት ሊያገኝ የሚችለው በቁጥር አንድ የተጠቀሰው ብሄራዊ ሪፎርም በሕዝቡ ተቀባይነት ካገኘ ብቻ ነው ።

አራት፣ ከትህነግ ጋር የሚደረግ ድርድር
ይህ መንግስት ትህነግ ድርድር ሊሳካ የሚቻለው መንግስት በአገርም ውስጥና በዲያስፖራ የነበረውን ድጋፍ መልሶ ለማግኘት ከቻለ ብቻ ነው ። መንግስት በተከታታይ የሰራቸውን ስህተቶች በግልጽ እና በቅንነት ለህዝብ ነግሮ በቁጥር አንድ ያለውን የብሄራዊ ሪፎርም ፕላን አጥጋቢና ህዝብ በሚቀበለው ጥልቀት ካቀረበ ብቻ ነው ።




Right
Member
Posts: 2824
Joined: 09 Jan 2022, 13:05

Re: ሱሊማን አብደላ፤ የአቢይ አህመድ መንግስት ከውድቀት ለመዳን ማድረግ ያለበት 4 ነገሮች

Post by Right » 12 May 2022, 07:22

Way too late.

People are desperately trying to rescue the leaky boat they are on board.

Basically this is the same advise we gave generously when all this started.

Post Reply