*****************************
የፀጥታው ግብረ ሀይል ምክር ቤት በወቅታዊ የሀገሪቱ የፀጥታ ሁኔታ ዙሪያ ውይይት አድርጓል፡፡
ምክር ቤቱ በቀጣይ መሠራት ያለባቸው አቅጣጫቻዎችንም አስቀምጧል፡፡
አሸባሪው ህወሓት አሁን ላይ ያለበት ሁኔታ መገምገሙን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ተመስገን ጥሩነህ ተናግረዋል፡፡
ከአሸባሪ ቡድኑ ጥፋት ጋር በተያያዘ ህወገጥ የመሣሪያ ዝውውር እና ኢ መደበኛ አደረጃጀቶች እየተፈጠሩ መሆኑን የፀጥታ ግብረ ሀይሉ መገምገሙን ዋና ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡
በኢመደበኛ ሀይሎች ላይ በጥናት ላይ ተመስርቶ አስፈላጊው እርምጃ እንደሚወስድም የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ተናግረዋል፡፡
የመከላከያ ሚኒስትሩ ዶ/ር አብርሃም በላይ፣ ሀገራዊ እና ቀጠናዊ ጉዳዮችን በመገምገም እና ከጐረቤት ሀገሮች ጋር ያለውን ግንኙነት ማጠናከር እንደሚገባ መገምገሙን ተናግረዋል፡፡
የፀጥታ ኃይሉም አሁን ላይ በሁሉም መስክ በዝግጅት ላይ መሆኑንም የመከላከያ ሚኒስትሩ ገልጸዋል፡፡
Please wait, video is loading...