ይህ ልጅ ስሙ ሳሊም መሀመድ ይባላል። የወሎ ኦሮሞ የከሚሴ የደዌ ሰፈር ነዋሪ ነው። የከሚሴ ጤና ጣቢያ አንቡላንስ ሾፌር ነበር።
ሳሊም - ባለፈው አመት ከ19/03/2021 ጀመሮ የረመዳንን ወር ጭምር ለሁለት ወራት ገደማ የአማራ ክልል የአማራ ልዩ ሃይልን እና ሚሊሻን አዝምቶ የወሎ ኦሮሞዎችን ንብረት እና በሺ የሚቆጠሩ ቤቶችን ማቃጠሉ፣ ከ300 በላይ ኦሮሞዎችን ገድሎ ወደ 600 ኦሮሞዎችን ገደማ ማቁሰሉ ይታወቃል።
በዚያን ወቅት ሳሊም መሀመድ በአንቡላንስ በመታገዝ ከጓደኞቹ ጋር በመሆን ቁስለኞችን ወደ ጤና ተቋም በማመላለስ ከሞት አትርፏል። ሳሊም በዝህ ተግባሩ የብዙ የሰዎችን ህይወት በመታደጉ ጥርስ ሲነከስበት ቆይቷል።
ሳሊም መሀመድ በ09/12/2021 ከሚሴ በእናቱ ሱቅ ፊት አቅራቢያ እያለ የከሚሴ ዞን ምክትል ሊቀመንበር በነበረው አሜ ሙሄ ይጠረዋል። ሳሊምም ወደ አሚ ሙሄ ይጠጋል። አሚ ሙሄም ወንድማዊ በሚመስል መልኩ ሳሊምን አቀፍ አርጎ ይዞት ይሄዳል።
ከጥቂት እርምጃዎች ቡሃላ የሳሊም ወላጅ እናት እያዪ አሚ ሙሄ በጥፊ በርግጫ ሳሊምን ይደበድበዋል። በመቀጠል የምታደርጉትን አድርጉት በማለት የመከላከያ ልብስ ለለበሱ የአማራ ልዩ ሃይሎች ሳሊምን አስረክቧል። ከዛን ቀን ጀምሮ እስካሁኗ ሰአት ድረስ ሳሊም መሀመድ በህይወት ይኑር አይኑር በህይወት ካለም የት እንዳለ አይታወቅም።
ጓደኞች እና ቤተሰቦቹ አዋሽ እስር ቤትን ጨምሮ የወሎ ኦሮሞዎች ታሰረዋል በሚባል እስር ቤቶች ሁሉ ቢያጠያይቁም ሳሊም መሀመድ የት እንዳለ መረጃ ለማግኘት አልቻሉም።
https://www.facebook.com/permalink.php? ... 6242472788
ወሎ
ኦቦ ሀሰን ቶልቻ ( የወታደር ልብስ የለበሱት በርግጫ የሚመቷቸው ሸማግሌ) ቦርከና ወንዝ ድልድይ አካባቢ ገድለዋቸው ሬሳቻው ተገኝቷል። ሴቷን ልጅ /ሰአዳን ጨምሮ የተቀሩትን እስካሁን የት እንደደረሷቸው አይታወቅም።
Please wait, video is loading...