Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 10186
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

"ታጥቀው ጫካ ያሉ ወገኖች ግጭቶችን በምክክር እንዲፈቱ: መንግስትም ይህንኑ ጥሪ ተቀብሎ ሁኔታዎችን እንዲያመቻች እንጠይቃለን" ከመላ አገሪቱ የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች (EBC)

Post by sarcasm » 15 Jan 2022, 19:35

ከመላ አገሪቱ የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎችና የሰላም እናቶች በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መከሩ
*******************


ከመላ አገሪቱ የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎች እና የሰላም እናቶች ዛሬ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት ካደረጉ በኋላ ባለ ስድስት ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል።

የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎች እና የሰላም እናቶች በአቋም መግለጫቸው ጦርነት በተካሄደባቸው የሀገሪቱ ክልሎች በደረሰው ሞት፣ ውድመት እና መፈናቀል የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እንገልጻለን ብለዋል።

ሁሉም አካላት በጦርነቱ የተጎዱ ክልሎችን መልሶ ለመገንባት እና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ እናደርጋለን ነው ያሉት።

በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል የተፈጠረውን መቃቃር ለመፍታት የአገራዊ ምክክር መድረኩ ትልቅ ሚና እንዲጫወት ጥሪ እናቀርባለን ብለዋል።
መንግስት እስረኞችን በመፍታት በአገሪቱ ሰላም እንዲያሰፍን በተደጋጋሚ ያደረግነውን ጥሪ ተቀብሎ በእስር ላይ የነበሩ የተወሰኑ ሰዎችን ክስ ማቋረጡ ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል፤ በመሆኑም የመንግስትን እርምጃ እያደነቅን አሁንም በጀመረው አኳኋን አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ ክልሎችም ይህንኑ መንገድ እንዲከተሉ ጥሪ እናቀርባለን ብለዋል።

በቅርቡ ከእስር የተፈቱት ግለሰቦችም በበኩላቸው የተጀመረው የሰላም መንገድ እውን እንዲሆን የየራሳቸውን በጎ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ እናቀርባለን ብለዋል።
እኛ የሃገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎች እና የሰላም እናቶች በአገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ሁሉም ታጥቀው ጫካ ያሉ ወገኖች ወደ ሰላማዊ መድረክ ተመልሰው ግጭቶችን በምክክር እንዲፈቱ ጥሪ እናደርጋለንም ብለዋል።

መንግስትም በበኩሉ ይህንኑ ጥሪ ተቀብሎ ሁኔታዎችን እንዲያመቻች እንጠይቃለን ማለታቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

ከላይ የተዘረዘሩት የሰላም ውጥኖች እውን እንዲሆኑ እና ዘላቂነት እንዲኖራቸው 11 አባላት ያሉት አገር አቀፍ የሰላም ቡድን ማቋቋማቸውንም የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎችና የሰላም እናቶች ይፋ አድርገዋል።
Please wait, video is loading...

Abere
Senior Member
Posts: 11128
Joined: 18 Jul 2019, 20:52

Re: "ታጥቀው ጫካ ያሉ ወገኖች ግጭቶችን በምክክር እንዲፈቱ: መንግስትም ይህንኑ ጥሪ ተቀብሎ ሁኔታዎችን እንዲያመቻች እንጠይቃለን" ከመላ አገሪቱ የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች (EBC)

Post by Abere » 15 Jan 2022, 19:51

Too late too little. This opportunity was slapped by TPLF 3 years ago, now 85 % of the population Ethiopia does not even to see eye-to-eye with TPLF and OLF. How is TPLF going to come to Addis Ababa, via Dessie, via Semera, via Gondar?????? Please grass and leaves on top it, to save TPLF. First of, the institution of elderly has been destroyed along time ago irreplaceably. It is gone forever. Are we talking Professor Isaac? hahahaha. The truth is only war will solve the Ethiopian situation. There will not be peace unless brought by defeating the blood thirsty TPLF. This is just a noise, it will remain hanging on the air. When the lion cub and the calf of a cow play in the field together, then any TPLF thug will cross the Amhara and Afar land and be the bedfellow of the so-called government. Total blockade for criminal TPLF and revenge!!!!

tolcha
Member
Posts: 3585
Joined: 27 Feb 2013, 16:51

Re: "ታጥቀው ጫካ ያሉ ወገኖች ግጭቶችን በምክክር እንዲፈቱ: መንግስትም ይህንኑ ጥሪ ተቀብሎ ሁኔታዎችን እንዲያመቻች እንጠይቃለን" ከመላ አገሪቱ የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች (EBC)

Post by tolcha » 15 Jan 2022, 21:55

sarcasm wrote:
15 Jan 2022, 19:35
ከመላ አገሪቱ የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎችና የሰላም እናቶች በወቅታዊ ጉዳይ ላይ መከሩ
*******************


ከመላ አገሪቱ የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎች እና የሰላም እናቶች ዛሬ በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት ካደረጉ በኋላ ባለ ስድስት ነጥብ የአቋም መግለጫ አውጥተዋል።

የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎች እና የሰላም እናቶች በአቋም መግለጫቸው ጦርነት በተካሄደባቸው የሀገሪቱ ክልሎች በደረሰው ሞት፣ ውድመት እና መፈናቀል የተሰማንን ጥልቅ ሃዘን እንገልጻለን ብለዋል።

ሁሉም አካላት በጦርነቱ የተጎዱ ክልሎችን መልሶ ለመገንባት እና ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ በትብብር እንዲሰሩ ጥሪ እናደርጋለን ነው ያሉት።

በተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል የተፈጠረውን መቃቃር ለመፍታት የአገራዊ ምክክር መድረኩ ትልቅ ሚና እንዲጫወት ጥሪ እናቀርባለን ብለዋል።
መንግስት እስረኞችን በመፍታት በአገሪቱ ሰላም እንዲያሰፍን በተደጋጋሚ ያደረግነውን ጥሪ ተቀብሎ በእስር ላይ የነበሩ የተወሰኑ ሰዎችን ክስ ማቋረጡ ለሰላም ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል፤ በመሆኑም የመንግስትን እርምጃ እያደነቅን አሁንም በጀመረው አኳኋን አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ ክልሎችም ይህንኑ መንገድ እንዲከተሉ ጥሪ እናቀርባለን ብለዋል።

በቅርቡ ከእስር የተፈቱት ግለሰቦችም በበኩላቸው የተጀመረው የሰላም መንገድ እውን እንዲሆን የየራሳቸውን በጎ አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ እናቀርባለን ብለዋል።
እኛ የሃገር ሽማግሌዎች፣ አባገዳዎች እና የሰላም እናቶች በአገራችን ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ሁሉም ታጥቀው ጫካ ያሉ ወገኖች ወደ ሰላማዊ መድረክ ተመልሰው ግጭቶችን በምክክር እንዲፈቱ ጥሪ እናደርጋለንም ብለዋል።

መንግስትም በበኩሉ ይህንኑ ጥሪ ተቀብሎ ሁኔታዎችን እንዲያመቻች እንጠይቃለን ማለታቸውን ኤፍቢሲ ዘግቧል።

ከላይ የተዘረዘሩት የሰላም ውጥኖች እውን እንዲሆኑ እና ዘላቂነት እንዲኖራቸው 11 አባላት ያሉት አገር አቀፍ የሰላም ቡድን ማቋቋማቸውንም የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳዎችና የሰላም እናቶች ይፋ አድርገዋል።
Please wait, video is loading...

The country is run by psychopaths. Who dares to talk to these psychopaths; only bullets talks well. So, better to push the war than “qiraqinbo selamwi mikikir”.

Post Reply