==========================================================================================================
==========================================================================================================
Ethiopian Press Agency /የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/
alS7306u76ho0fcltled ·
“በድል የታጀበው የመጀመሪያው ምእራፍ” በሚል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ያስተላለፉት መልዕክት ዋና ዋና ነጥብ ‼
ኢትዮጵያን መገዳደር ይሞከር ይሆናል። ተገዳድሮ ማሸነፍ ግን ትናንትም አልተቻለም፤ ዛሬም አይሆንም፤ ነገም አይቻልም፤
ኢትዮጵያ የሚለው ስም ሁሌም ከአሸናፊነት ጋር የተያያዘ ነው፤
ከጥቂት ጊዜያት በፊት ኢትዮጵያን ሊወጋ የተነሳውን ጠላት በጋራ ሆነን እንድንመክት ጦር ግንባር ላይ የያዝነው ቀጠሮ ጠላትን አንገት ሲያስደፋ ኢትዮጵያን ቀን አድርጓታል፤
ሀገራችን ታፍራና ተከብራ እንድትኖር ለማድረግ በጦር ግንባር እየተከፈለ ያለው መስዕዋትነት የኢትዮጵያን የአሸናፊነት ስም የሚመልስ መሆኑን አበስራለሁ፤
ያቀረብኩትን ጥሪ ተቀብላችሁ ሕይወታችሁን፣ ጉልበታችሁን፣ ሀብታችሁን፣ ዕውቀታችሁን፣ ጊዜያችሁንና ሞያችሁን ለሠጣችሁ ሁሉ በኢትዮጵያ ስም ላመሰግናችሁ እወዳለሁ፤
የመጀመሪያውን ምእራፍ አጠናቅቄ ለተወሰኑ ጊዜያት ወደ ቢሮ መመለሴን እገልጻለሁ፤
ዛሬም ሆነ ወደፊት ጠላቶቻችን ጉልበታቸው ዝሎ፣ የጥላቻና የጠበኝነትን መንገድ ጥለው፣ የፍቅርና የሰላምን መንገድ እስኪመርጡ ትግላችን ይቀጥላል፤
የእኛ ፍላጎት ሁሌም ሰላምና ፍቅር ነው፤
ነገሮች ያለቁና የተጠናቀቁ እስኪመስሉ ድረስ ኢትዮጵያን የማያውቁ ሁሉ በሥጋትና በፍርሐት ተውጠው ነበር፤
ሠግተው ሊያሠጉን፤ ፈርተው ሊያስፈራሩን የሞከሩ የውስጥና የውጭ አካላትም ነበሩ፤
የኢትዮጵያን የአሸናፊነት ምሥጢር የሚያውቁት ብቻ በጽናት እስከ መጨረሻው የቆሙበት አጋጣሚም ተፈጥሮ ነበር፤
ወደ ትግል የገባነው ሐቅን ይዘን ነውና የኢትዮጵያ አምላክ እንደ ወትሮው ከእኛ ጋር ነበር፤
ልባችንን አጀግኖ የኢትዮጵያን አሸናፊነት በዓይናችን አሳይቶናል፤
ውድቀታችንን ሲመኙ የነበሩትን ሁሉ አሳፍሮ ዳግም የኢትዮጵያን ስም በወርቅ ቀለም እንድንጽፍ አስችሎናል፤
ማንም ተነስቶ ኢትዮጵያን ማውረድ ከማይችልበት ማማ ላይ እየሰቀልናት ነው፤
ከገጠመን ፈተና ይልቅ በዕድሎቻችን ላይ አተኩረን ከሠራን ኢትዮጵያን ኃያልና ራሷን በሁሉም መስክ የቻለች ሀገር እናደርጋታለን፤
ከፈጣሪ ቀጥሎ በፈተናችን ጊዜ አብረውን ለቆሙ እና በዓለም አደባባይ ለተማገቱልን ሁሉ ኢትዮጵያ ከፍ ያለ ምስጋና ታቀርባለች፤
በህልውና ዘመቻው ወቅት ያየነውን የኢትዮጵያውያንን አንድነት እስከ ዓለም ፍጻሜ ሀብታችን አድርገነው መቀጠል አለብን፤
ትግሉ ገና አልተጠናቀቀም። ነጻ ያልወጡ አካባቢዎች አሉን፤
የተበተነው ጠላት እንዲማረክ ማድረግ አለብን፤
አካባቢያችንን ከበፊቱ በበለጠ ነቅተን የመጠበቂያ ጊዜው አሁን ነው፤ ፍተሻና አሰሳዎችን አጠንክረን መቀጠል ይገባናል፤
አሁን የፈተነን ኃይል ዳግመኛ የኢትዮጵያ ፈተና ሆኖ እንዳይመጣ የሚያስችል ዘላቂ መፍትሔ ልንሰጠው ይገባል፤
በተጋድሏችን ያገኘነውን ነገር ለማቅለል የሚፈልጉትን ፊት እንንሣቸው፤
በጋራ ታግለን በጋራ ያስገኘነውን ድል፣ እንደ ቅርጫ ሥጋ ሊመድቡ የሚነሡትን አቃራጮች እናነውራቸው፤
ያሸነፈችው ኢትዮጵያ ናት፤ ከዚህ የወረደ ነገር አንቀበልም፤