Natnael Mekonnen
33m ·
" ... በራሳቸው ምክንያት ካልሆነ በስተቀር የአየር ድብደባውና የሰብአዊ እርዳታ ጫኝ አውሮፕላን እንቅስቃሴ አይገናኝም " - ዶ/ር ለገሰ ቱሉ
#Ethiopia : ዛሬ ሮይተርስ 2 የሰብአዊ እርዳታ ሰራተኞችን ጠቅሶ እንደዘገበው፤ የተመድን የሰብአዊ እርዳታ የጫነ አውሮፕላን መንግስት በትግራይ ክልል ባካሄደው የአየር ድብድባ ምክንያት መቐለ ማረፍ አልቻለም ብሏል።
ሮይተርስ በዚህ ጉዳይ ሁለት ሰማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ሰዎችን ማናገሩን ጠቅሷል።
ይህንን ጉዳዩን በተመለከተ ለአል ዐይን ቃላቸውን የሰጡት የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) ፥ " በራሳቸው ምክንያት ካልሆነ በስተቀር የአየር ድብደባው እና የሰብአዊ እርዳታ ጫኝ አውሮፕላን እንቅስቃሴ አይገናኝም" ብለዋል።
“አንደኛ ሰዓቱ የተለያየ ነው” ያሉት ዶ/ር ለገሰ፤ “መዳረሻዎችም የተለያዩ ናቸው” ሲሉም ተናግረዋል።
-
- Senior Member+
- Posts: 33103
- Joined: 26 Feb 2016, 13:04