=========================================================================================================================
Natnael Mekonnen
1htSnfso0t ·
ሰበር ዜና
የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ዛሬ ተጨማሪ የአየር ጥቃት ፈፅሟል።
#Ethiopia : የዛሬው የአየር ድብደባ የትግራይ ነፃ አውጪ ግንባር (TPLF) የማሰልጠኛ ማዕከል መሆኑን በፌዴራል መንግስት ስር ያለው የወቅታዊ ሁኔታ መረጃ ማጣሪያ ገፅ አሳውቋል። ገፁ የአየር ድብደባው የት እንደተፈፀመ በግልፅ ባይጠቅስም " ሌላው የአሸባሪው ቡድን የህወሓት ማሰልጠኛ ማዕከል ዛሬ የአየር ጥቃት ዒላማ ሆኗል" ሲል ገልጿል። አክሎም "ይህ ማዕከል ለአሸባሪው ቡድን ወታደራዊ ሥልጠና ከመዋሉ በፊት የኢፌዴሪ መከላከያ ማሠልጠኛ ማዕከል ነበር በአሁኑ ወቅት አሸባሪው ቡድን በዚህ ተቋም ውስጥ ወታደራዊ ስልጠና የሚሠጥበት፤ የዉጊያ ግንኙነት ኔት ወርክ ያለበት ነው" ብሏል።
ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችና ምስል ቪዲዮ ለመመልከት ቴሌግራም https://t.me/NatnaelMekonnen21