ይሁንና አቶ ገዱ በግለሰብ ደረጃ ሥልጣን ባይሰጣቸውም መቼም እሳቸው አንበሳ ናቸው አማራ ክልል ላይ ግን ሥርዎ መንግስታቸውን ለማስቀጠል ሲለፉ ከርመው ተሳክቶላቸዋል። የአቶ ገዱ ሥርወ መንግስት ከክልል አልፎ በዞን ደረጃ የውሳኔ ሰጭ ሹመቶችን በእጁ አስገብቷል። በክልሉ የሁሉም ዞኖች ሹመት የአቶ ገዱ እጅ አለበት። እስከ ዛሬም የእሳቸው ሥርዎ መንግስት ስለነበረ አሁንም ከሰወቹ መለዋወጥ በቀር የእሳቸው ሥርወ መንግስት ስለቀጠለ አዲስ ለውጥ ይመጣል የተሻለ የመንግስት ሥርዓት ይኖራል ብዬ ተስፋ አላደርግም። ችግሩን በፈጠረው አስተሳሰብ ችግሩን መፍታት አይቻልም። አቶ ገዱ ግን የብአዴኑ ስብሀት ነጋ ለመሆን ችለዋል።
Please wait, video is loading...