Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Abdisa
Member+
Posts: 5747
Joined: 25 Apr 2010, 19:14

በሱዳን እየተካሄደ ያለው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ግብፅን ጭምር ስጋት ላይ የሚጥል ነው ተባለ

Post by Abdisa » 21 Sep 2021, 09:45

በሱዳን የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ተካሄደ

On Sep 21, 2021



የሱዳን መንግስት ላይ የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ መካሄዱን የሀገሪቱ መንግስት ሚዲያ አስታውቋል።

በተለያዩ ሚዲያዎች አሁን እንደተዘገበው ማንነታቸው ያልተገለጸው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ያደረጉ አካላት በካርቱም ኦምዱርማን የሚገኙትን የሀገሪቷን የሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ጣቢያዎች ለመቆጣጠር ሙከራ ማድረጋቸውም ነው የተገለፀው፡፡ መንግስት ሁኔታውን ለመቆጣጠር ጥረት እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።

በአሁኑ ሠዓት ታንኮች ወደ ኦምዱርማን ድልድይ እና ወደ ሀገሪቷ ፓርላማ ህንፃ ተጠግተው መንገዱን በመዘጋት እንደተቆጣጠሩት ሲገለፅ በአካባቢው የጸጥታ አካላት እንደተሰማሩም ነው የተመላከተው፡፡

በካርቱም የሱዳን የጸጥታ አካላት ናይልን ከኦምዱርማን የሚያገናኘውን ድልድይ ቢዘጉም፣ በአካባቢው ሁኔታዎች ተረጋግተው እንቅስቃሴዎች እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ መቀጠላቸው ነው የተሰማው፡፡





Abdisa
Member+
Posts: 5747
Joined: 25 Apr 2010, 19:14

Re: በሱዳን እየተካሄደ ያለው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ግብፅን ጭምር ስጋት ላይ የሚጥል ነው ተባለ

Post by Abdisa » 21 Sep 2021, 10:24

የሱዳኑ ጁንታ እሳት ለኩሶ ከዳር ሆኖ መመልከት ወይም ቁጭ ብሎ መሞቅ እንደማይቻል ከህወሓትና ድርጊቱ መማር አለበት።


Digital Weyane
Member+
Posts: 8473
Joined: 19 Jun 2019, 21:45

Re: በሱዳን እየተካሄደ ያለው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ ግብፅን ጭምር ስጋት ላይ የሚጥል ነው ተባለ

Post by Digital Weyane » 21 Sep 2021, 13:09

ጁንታው ዎንድሜ eden/Sarcasm ስልክ ደውሎ በሱዳን የተሞከረውን መፈንቅለ መንግስት <<ኡኔ ነው ያከሸፍኩት!>> ብሎ ሲነግረኝ እጅግ ከመገረሜ የተነሳ ማመን እንኳ ተስኖኛል። ዎደ ውጭ አገር የሸሹ ጁንታ ዎገኖቼ ከኢትዮጵያ ህዝብ በዘረፉት ብር ሃምበርገር ኡየጎመጡ፣ ዊስኪ ኡየተጎነጩና፣ እስትሪፕ ክለብ ኡያደሩ እጅግ የሚያስገርሙ በርካታ ታላላቅ ተግባራትን ይፈፅማሉ ብዬ አልጠብቅም ነበር። አይ ዎዝ ሮንግ! :roll: :roll:

Post Reply