Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
-
Meleket
- Member
- Posts: 3057
- Joined: 16 Feb 2018, 05:08
Post
by Meleket » 18 Sep 2021, 05:02
እየተዝናናን እንማማር!
ስለዚህ መጠሐፍ አስቀድሞ አንዱ ወንድማችን እዚሁ መረጃ ላይ አጋርቶን ነበር። እናመሰግነዋለን። ቀደምቶቻችን “ባህ ክብላ ዱባ ጽብሓላ” እንዲሉ እስቲ አንዳንድ ኤርትራዊ እይታችንን ለደራሲው ይዘንድር ኪዴ መንገሻ እንጠቁመው! ታሻውም ለነራስ መንገሻ ልጆች ያካፍላቸው። ጨዋታችን ስለ መናገሻዋ ጎንደር ነው!
“የአባታችን የኖኅ መቃብር በክመንቶች ምዝገኒ ድግና (አሁን ጎንደር ከተማ ውስጥ የፋሲል ግንብ የተሰራበት ቦታ) የሚገኝ ሲሆን የባለቤቱ የእሜቴ አይከል መቃብር ደግሞ የጭልጋ ወረዳ ዋና ከተማ በሆነችው አይከል ከተማ ውስጥ እስከ አሁን ድረስ ተጠብቆ ይኖራል።” ገጽ 2-3 [ድግና የምትለውን ቃል ያዝልኝ እንዳትለቃትማ የምለው አለኝ! ኤርትራ ውስጥ አከለጕዛይና ሰራዬ በተባሉ አውራጃዎች ውስጥ “ወረዳ ደቂ ድግና” ማለትም “የድግና ልጆች ወረዳዎች” በመባል የሚታወቁ ሁለት ወረዳዎች አሉ። እነዚህን ሁለት ወረዳዎች ያፈራው፡ ድግናይ የተባለው ከነገደ ማሉቕ አምስት የአከለጽዮን ልጆች አንዱ ነው። . . . በአከለጕዛዩዋ “ደቂ ድግና” የሚካተቱት ቀዬዎች ድግሳ፣ ዓዲ ሓዲድ፣ ዓዲ ቀሪጭ፣ ማይ ወይኒ፣ ሓዲሽ ዓዲ ቡግነይ፣ ዓዲ አውሒ ሺምሔል ሲሆኑ፤ በሰራዬዋ “ደቂ ድግና” ደግሞ ከብታ፣ ጊናባለ፣ ዓዲ ኣብርሃም፣ ዓዲ ኣኮሎም፣ ጸበላ፣ ሓሰር ኣልቦና ገዳም እንዳቦና ይገኙበታል። ይላሉ የኤርትራ ህዝብ ትውልድ ታሪኽ በሚል ርእስ መጠሐፍ የጣፉት መሪጌታ ብርሃነመስቀል ተስፋማርያም በገጽ 197-199]
“የጥንት ክመንቶች በጣም ጎልተው የሚታወቁ ሦስት የአስተዳደር፣ አምልኮትና ማህበራዊ አስተምህሮ ማዕከላት ነበሯቸው። . . . እነዚህ ማዕከላት የየራሳቸው ወንበሮች የነበራቸው ሲሆን፣ ተጠሪነታቸው ማዕከሉን አዅሱም ላይ አድርጎ ለነበረው የበላይ ወይም ጠቅላይ ወንበር ነበር። ይህ የበላይ ወይም ጠቅላይ ወንበር “እንበረም” በመባል ይታወቃል (ኤርሚያስ ከበደ፣ 1993 ፤ ያሬድ ግርማ፣ 1999። እነዚህ ማዕከላት የሃይማኖት አስተምህሮ፣ የባርኮት፣ የቅድስና፣ የመንፈሳዊ አስተዳደር፣ ወዘተ ማዕከላት ሆነው ለረጅም ዘመናት አገልግለዋል። በእነዚህ አካባቢዎች ዛሬ ድረስ ዘልቀው የሚታዩ ታሪካዊ ማስረጃዎች ይህን ይመሠክራሉ።” ገጽ 5 [ኤርትራችን ውስጥ ምጥዋ አጠገብ “እምበረሚ” የምትባል ቀዬ አለችን አቡነ እንበረም የነበሩባት ስፍራ እንደሆነችም ሲነገር እንሰማለን። እንግዲህ ማን ያውቃል ኣዅሱምንም ክርስትና እንድትቀበልና እንድትጠመቅ የሆነችው በእንበረሚ በኩል ሊሆን ይችላል። ድሮውንስ ቢሆን ድባርዋ አካባቢ አሁን የሰማእታት መቃብር በሚገኝበት “ምስላም” ማለትም “መሸለም” በተባለው ኮረብታ፡ ኢዛናና ሳይዛና ሹመታቸው ጠድቆ በዓለ ሽመታቸው ተከብሮላቸው እንደነበር የሚነገረው መች ውሸት ሆነና!]
“ክመንት የኢትዮጵያ ታሪክ የምስጢር ቁልፍ ነው” ገጽ 26 [የጦቢያ ታሪክ ከ80 በላይ የምስጢር ቁልፎች እንዳለው ሲነገርም ሰምተናል። ስለዚህ ክመንት ከነዚህ ውስጥ አንዱ እንደሆነ አውቀናል።]
“. . . አብዛኞቹ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት ቦታዎች፣ ወንዞች፣ ተራሮች፣ ሐይቆች፣ ጅረቶች፣ ሸለቆዎች ወዘተ በክመንታ ቋንቋ ብቻ ተሰይመው የምናገኛቸው። ሸዋ ውስጥ ያሉ አያሌ የቦታ ስያሜዎች ራሱን ሸዋን ጨምሮ፣ ቡልጋ፣ ምንጃር፣ አንኮበር፣ አንጐት፣ መንዝ፣ አሳግርት፣ እቲሳ፣ ቀወት፣ ወዘተ የሚሉት ሁሉም የክመንት ቋንቋ ስያሜዎች ናቸው (ሰማልኝ፣ 2010)።” ገጽ 53 [ይገርማል፡ ስያሜዎችን ከነትርጉማቸው ብታቀርበው ኖሮ ይበልጥ ግሩም ነበር!]
“ . . . ሁልጊዜ ቅማንቶች በተቀደሱ ዛፎች (ድግናዎች) ውስጥ ሆነው አምልኮታቸውን ያከናውናሉ። . . .ገጽ 79 [ድግናዎች ማለት የተቀደሱ ዛፎች ማለት ነዋ በክመንትኛ ድንቅ ነው! ኤርትራ ውስጥ ያሉት ደቂ ድግና የተባሉት የአከለጕዛይ ቀዬዎች አካባቢ ብዙም ሳይርቅ፡ ደራሲው ይዘንድር ኪዴ መንገሻ መጸሐፉ ሽፋን ላይ ያስቀመጠው ዓይነት በርካታ የዋርካ ዛፎች ይገኛሉ፡ አንዷም በኤርትራ የአምስት ብር(ናቕፋ) ላይ ተስላ ትገኛለች። ይህ ታሪካዊ ስፍራም እንደመሰዊያው ዓይነት የመስዋእት ድንጋዮች እንደነበሩበት ሲነገርም ሰምተናል። ያው እንግዲህ ሕገ ልቦናው በዚህ በኩልም ነበር ለማለት ነው! ]
“ . . . ውስጥ ለውስጥ የሚፈጠሩ ችግሮች ቢኖሩም አያሌ የክመንት አባቶችና የታሪክ ጸሐፍት እንደሚሉት ከሆነ ክመንቶች አንጻራዊ መረጋጋትና ሠላም ያገኙት በዚህ በጐንደር ሥርዎ መንግሥት ዘመን ነበር። ከዛ ፊት የነበሩት ፈታኝ የመከራ ዘመኖች ናቸው። በወሎ፣ በጎጃም፣ በሸዋ፣ በበጌምድር፣ በስሜን በትግራይና ኤርትራ የነበሩ ክመንቶች በሃይማኖታቸው ምክንያት ከባድ መከራ ውስጥ ወድቀው ቆይተዋል። . . . ”ገጽ 94 [ኤርትራ ውስጥም ክመንቶች ነበሩ ማለት ነውን? ድሮውንስ ቢሆን የኤርትራ ደጋማ ክፍል ነዋሪዎች ብዙዎቹ የዘር ሃረጋቸውን ደንቢያን በመጥቀስ እማደል የሚገልጹት! ስንቷ ኤርትራዊም አይደለች ጎንደር ድረስ እየሄደች ያያቷን መቃብር ያየች!]
“በክመንት ሕዝብ ላይ ሙሉ መጽሐፍ የጻፈው የክመንት ትግል መሥራች ክቡር አቶ ነጋ ጌጤ (1993) ሲሆን፣ በድፍረት ስለ ክመንት ሕዝብ እውነታውን ጽፎታል።” ገጽ 112 ። [ታድያ ለገንዘብ ሳይሆን ለእውቀት ከተጣፈ የፋርማሲስቱን የአቶ ነጋ ጌጤን መጠሐፉ ይዘት በሙሉ እዚህ አምጡትና እናንበዋ። አቶ ነጋ በንጉሱ ዘመንና በደርጉ ግዜ ትንፍሽ ሳይል በወያኔ ጊዜ ድፍረት አግኝቶ ስለክመንት ሕዝብ የጻፈ “ደፋር” ጠሐፊ ነው! ለማንኛውም እንኳን ጣፈ!!!]
እንግዲህ ያኔ “ኤርትራ ሰሜን ጉራጌ ናት!” እንደተባለው ሁሉ ብሮባጋንዲስቶች “ኤርትራ ሰሜን ክመንት ናት!” በሉና አዝናኑና!
-
Wedi
- Member+
- Posts: 7983
- Joined: 29 Jan 2020, 21:44
Post
by Wedi » 18 Sep 2021, 05:29
ፋሽሽት ትግሬዎች እንኳን ለክማንት ህዝብ ለራሳቸው ለትግሬ ህዝብ ዴንታ የላቸው!! አላማቸው ህዝብ ማስጨረስ እና ሰላም መንሳት ብቻ ነው!!
ክማንት የፋሽሽት ትግሬዎች ፕሮጀክት እንደሆነ ለማውቅ ከፈልክህ ከታች በአቻም የለህ ታምሩ የተጻፈውን ተጨባጭ መረጃ ከታች አንብብ!!
ይህችን አንብባት!!
**************************************************************************************
Achamyeleh Tamiru
Sept 1 2021
ፋሽስት ወያኔ ከ92 ሚሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ዓመታዊ ባጀት መድቦ፤ 605 ክላሽንኮቮችን፣ 40 የቡድን መሳሪያዎችን፣ 5272 ቦንቦችንና ሌሎች በርካታ የጦር መሳሪያዎችን አስታጥቆ የሚያንቀሳቅሳቸው የቅማንት ኮሚቴና ቅዴፓ!
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በኅዳር ወር መቀሌን ከተቆጣጠረ በኋላ በፋሽስት ወያኔ ይፋዊና ስውር ቢሮዎች ውስጥ በርካታ ፍተሻዎች ተካሂደው ነበር። በተካሄዱት ፍተሻዎችም ያልተገኘ የፋሽስት ወያኔ የ47 ዓመታት ገመናና ሚስጥራዊ ሰነድ አልነበረም ለአገርና ሕዝብ የሚቆረቆሩ የአገር ቤት ወዳጆቻችንም ከሚስጥራዊ ሰነዶቹ መካከል የተወሰኑትን አጋርተውን አንዳንዶቹን ለመመልከት ችለናል።
በእጃችን ከገቡት የፋሽስት ወያኔ ሚስጥራዊ ሰነዶች መካከል ፋሽስት ወያኔ ከ92 ሚሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ዓመታዊ ባጀት መድቦና እልቆ ቢስ የጦር መሳሪያ አስታጥቆ የሚያንቀሳቅሳቸው የቅማንት ኮሚቴና ቅዴፓ የሚባለውን ፓርቲ የወንጀል ስምሪት የሚያጋልጡ ሰንዶች ይገኙበታል።
አሳዛኙ ነገር በአቃቤ ሕግና ፌዴራል ፖሊስ ተብዮዎቹ እጅ ላይ የሚገኙንት እነዚህ የፋሽስት ወያኔ የወንጀል ሰነዶች እስከ ዛሬ ድረስ ለሕዝብ ይፋ አለመሆናቸው ብቻ ሳይሆን ፋሽስት ወያኔ በሺዎች የሚቆጠር ክላሽንኮቭ፣ ቦንብ፣ የቡድን መሳሪያ፣ ሌሎችን የጦር መሳሪያዎች አስታጥቆና በሺዎች የሚቆጠሩ ተዋጊ አባላቱን አሰልጥቶ በጎንደር ላይ ያሰማራው ቅዴፓ የሚባለው ፓርቲ ዛሬም ድረስ ብርቱካን ሜዴቅሳ በምትመራው የምርጫ ቦርድ መዝገብ ሰላማዊ የፖለቲካ ፓርቲ ተብሎ ተመዝግቦ መገኘቱ ነው።
የሆነው ሆኖ ከታች የሚታዩት ገጾች የቅማንት ኮሚቴና ቅዴፓ የሚባለው ፓርቲ ከፋሽስት ወያኔ ጋር የተዋዋሉትን የሚያሳይ ሲሆን ሰነዱ አማራን ማኅበራዊ እረፍት የመንሳት ፋሽስት ወያኒያዊ ተልዕኮ ተሰጥቷቸው የሚንቀሳቀሱት የቅማንት ኮሚቴና ቅዴፓ የሚባለው ፓርቲ ከመስከረም 1/2013 ዓ.ም. - እስከ መስከረም 1/2014 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ እውን እንዲያደርጉት መቀሌ ድረስ ተገኝተው የተቀበሉትን ስምሪትና ይህን ሰይጣናዊ አላማ በጦር መሳሪያ ለማስፈጸምም ፋሽስት ወያኔ የመደበላቸውን ከ92 ሚሊዮን ብር በላይ የሚሆን ጥሬ ገንዘብ ዓመታዊ ባጀትና 605 ክላሽንኮቭ፣ 40 የቡድን መሳሪያ፣ 5272 ቦንቦችን ጨምሮ ሌሎች እልቆ ቢስ የጦር መሳሪያዎችን አስታጥቆ ወደ ጎንደር እንደላካቸው የሚያሳዩ ናቸው።
ማሳሰቢያ፡-
ሰነዱ የተገኘው አቃቤ ሕግና ከፌዴራል ፖሊስ ከሚባሉት ቢሮዎች ሲሆን እኔ ዘንድ የደረሰው ለአገርና ሕዝብ በሚቆረቆሩ ወገኖቼ አማካኝነት ነው። እነዚህ ወገኖች ያጋሩኝ ሰነዶች በርካቶች ናቸው። በደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል ፊርማ ለነ ያየሰው ሽመልስ የተቦጨቀውን ረብጣ ገንዘብና ለሌሎች የፋሽስት ወያኔ ጉዳይ አስፈጻሚዎች የተሰጠውን ዳጎስ ያለ የብር መጠን የሚያሳዩ ሌሎች የመቀሌ ሰነዶችን ይዘን በሌላ ጊዜ እንመለሳለን።
Please wait, video is loading...
*************************************************************************************
Achamyeleh Tamiru
Sept 2 2021
ፋሽስት ወያኔ ከ92 ሚሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ዓመታዊ ባጀት መድቦ፤ 605 ክላሽንኮቮችን፣ 40 የቡድን መሳሪያዎችን፣ 5272 ቦንቦችንና ሌሎች በርካታ የጦር መሳሪያዎችን አስታጥቆ የሚያንቀሳቅሳቸው የቅማንት ኮሚቴና ቅዴፓ! [ክፍል ፪]
ትናንትና በክፍል አንድ ባቀረብሁት ጽሑፍ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት በዚህ ዓመት ኅዳር ወር ላይ መቀሌን ከተቆጣጠረ በኋላ በፋሽስት ወያኔ ግልጽና ስውር ቢሮዎች ውስጥ በተካሄዱ ፍተሻዎች ከተገኙ ሰነዶች መካከል የተወሰኑትን አጋርቼ ነበር።
በትናንትናው ጽሑፌ ካጋራኳቸው የፋሽስት ወያኔ ሚስጥራዊ ሰነዶች መካከል የቅማንት ኮሚቴንና ቅዴፓ የሚባለው ፓርቲ ከ92 ሚሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ዓመታዊ ባጀት ተመድቦላቸውና 605 ክላሽንኮቮች፣ 40 የቡድን መሳሪያዎች፣ 5272 ቦንቦችና ሌሎች በርካታ የጦር መሳሪያዎች እንዲታጠቁ ተደርጎ አማራን ማኅበራዊ ረፍት ለመንሳት ከፋሽስት ወያኔ ተልዕኮ ተቀብለው ወደ ጎንደር የተሰማሩበትና ተልዕኳቸውም ከመስከረም 1 ቀን 2013 ዓ.ም. - መስከረም 1 2014 ዓ.ም. ባለው አንድ አመት ጊዜ ውስጥ ለመፈጸም መስማማታቸውን የሚያሳየው ውል አንዱ ነበር።
በዛሬ ውለት የማጋራው መቀሌ ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካዔል ቢሮ የተገኘ ሰነድ ደግሞ የቅማንት ኮሚቴና ቅዴፓ የሚባለው ፓርቲ ፋሽስት ወያኔ የመደበላቸውን ከ92 ሚሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ዓመታዊ ባጀትና 605 ክላሽንኮቮችን፣ 40 የቡድን መሳሪያዎችን፣ 5272 ቦንቦችንና ሌሎች በርካታ የጦር መሳሪያዎችን ከፋሽስት ወያኔ ፈርመው የተቀበሉት የቅማንት ኮሚቴና ቅዴፓ የሚባለው ፓርቲ አባላትን ስም፣ ፊርማና የስልክ ቁጥራቸውን ሳይቀር በእጃቸው የጻፉበትን ሚስጥራዊ ሰነድ ነው።
እነሆ የሰዎቹ ስም ዝርዝር ከነ ሙሉ አድራሻቸው! እነዚህ ሰዎች ናቸው እንግዲህ ከፋሽስት ወያኔ የተመደበላቸውን ከ92 ሚሊዮን ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ዓመታዊ ባጀትና 605 ክላሽንኮቮችን፣ 40 የቡድን መሳሪያዎችን፣ 5272 ቦንቦችንና ሌሎች በርካታ የጦር መሳሪያዎችን ከመቀሌ ተረክበው ወደ ጎንደር የተሰማሩት!
በቀጣይ የምናወጣው በደብረ ጽዮን ገብረ ሚካዔል ተፈርሞ ለነያየሰው ሽመልስ እንዲከፈል የተደረገውን በሚሊዮኖች የሚቆጠር ጥሬ ገንዘብ የሚያሳየውን ሰነድ ነው።
Please wait, video is loading...
-
Meleket
- Member
- Posts: 3057
- Joined: 16 Feb 2018, 05:08
-
Wedi
- Member+
- Posts: 7983
- Joined: 29 Jan 2020, 21:44
Post
by Wedi » 18 Sep 2021, 06:01
-
Wedi
- Member+
- Posts: 7983
- Joined: 29 Jan 2020, 21:44
Post
by Wedi » 18 Sep 2021, 06:21
-
Wedi
- Member+
- Posts: 7983
- Joined: 29 Jan 2020, 21:44
-
Meleket
- Member
- Posts: 3057
- Joined: 16 Feb 2018, 05:08
Post
by Meleket » 20 Sep 2021, 03:54
-
Wedi
- Member+
- Posts: 7983
- Joined: 29 Jan 2020, 21:44
Post
by Wedi » 20 Sep 2021, 06:59
-
Meleket
- Member
- Posts: 3057
- Joined: 16 Feb 2018, 05:08
Post
by Meleket » 20 Sep 2021, 10:27