የወሩ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነጻጸር የ30 ነጥብ 4 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱም ተገልጿል
በተጠናቀቀው የነሐሴ ወር የነበረው አጠቃላይ የምግብ ዋጋ ግሽበት 37.6 በመቶ ሆኖ ተመዘገበ፡፡
የነሐሴ ወር 2013 ዓ/ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ነሐሴ ወር 2012 ዓ.ም ጋር ሲነፃፀር በ30.4 ከመቶ ከፍ ብሎ እንደነበርም አል ዐይን አማርኛ ከማዕከላዊ ስታትስቲክስ ያገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡
የዋጋ ግሽበት ሁኔታ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር በማነፃፀር የሚገኘው ውጤት ወቅታዊ የዋጋ ግሽበት ሁኔታን ይገልጻል፡፡
በዚህ መሰረት የምግብ ዋጋ ግሽበት የነሐሴ ወር 2013 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ነሐሴ ወር 2012 ዓ.ም ጋር ሲነፃፀር በ37.6 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡
በዳቦና እህሎች ላይ የታየው የዋጋ ጭማሪ በያዝነው ወር ተጠናክሮ የቀጠለም ሲሆን በተለይ የሩዝ፣ የእንጀራ፣ የዳቦ፣ የጤፍ፣ የስንዴ፣ የማሽላ፣ የበቆሎ፣ የገብስ፣ የስንዴ ዱቄት፣ የፓስታና ማካሮኒ ዋጋ በፍጥነት ጨምሯል፡፡
Continue reading https://am.al-ain.com/article/total-foo ... -of-august
-
- Senior Member
- Posts: 10186
- Joined: 23 Feb 2013, 20:08