Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 10186
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

አጠቃላይ የምግብ ዋጋ ግሽበት በተጠናቀቀው የነሐሴ ወር የ37.6 % ጭማሪ ማሳየቱ ተገለጸ!

Post by sarcasm » 09 Sep 2021, 06:50

የወሩ አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር ሲነጻጸር የ30 ነጥብ 4 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱም ተገልጿል

በተጠናቀቀው የነሐሴ ወር የነበረው አጠቃላይ የምግብ ዋጋ ግሽበት 37.6 በመቶ ሆኖ ተመዘገበ፡፡

የነሐሴ ወር 2013 ዓ/ም አጠቃላይ የዋጋ ግሽበት ካለፈው ዓመት ነሐሴ ወር 2012 ዓ.ም ጋር ሲነፃፀር በ30.4 ከመቶ ከፍ ብሎ እንደነበርም አል ዐይን አማርኛ ከማዕከላዊ ስታትስቲክስ ያገኘው መረጃ አመልክቷል፡፡

የዋጋ ግሽበት ሁኔታ ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወር ጋር በማነፃፀር የሚገኘው ውጤት ወቅታዊ የዋጋ ግሽበት ሁኔታን ይገልጻል፡፡

በዚህ መሰረት የምግብ ዋጋ ግሽበት የነሐሴ ወር 2013 ዓ.ም ካለፈው ዓመት ነሐሴ ወር 2012 ዓ.ም ጋር ሲነፃፀር በ37.6 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል፡፡

በዳቦና እህሎች ላይ የታየው የዋጋ ጭማሪ በያዝነው ወር ተጠናክሮ የቀጠለም ሲሆን በተለይ የሩዝ፣ የእንጀራ፣ የዳቦ፣ የጤፍ፣ የስንዴ፣ የማሽላ፣ የበቆሎ፣ የገብስ፣ የስንዴ ዱቄት፣ የፓስታና ማካሮኒ ዋጋ በፍጥነት ጨምሯል፡፡

Continue reading https://am.al-ain.com/article/total-foo ... -of-august