የቢዘኑ መንፈስ . . . [ሰሞንኛው ግርድፍ ኤርትራዊ ግጥም]
Posted: 25 Aug 2021, 02:57
የቢዘኑ መንፈስ [ሰሞንኛው ግርድፍ ኤርትራዊ ግጥም]
የኤርትራ ደጀን ያባሃኒ መንፈስ፣
የኤርትራ ግርማ የአዳሉ መንፈስ፣
የኤርትራ ምሽግ የደንደኑ መንፈስ፣
የኤርትራ ዋልታ የቢዘኑ መንፈስ፣
ያገሬን ጠላቶች ሚደመስስ፣
ያገሬን ልጆች ልብ፡ ሚያረሰርስ፣
ማነው የምትሉ፡ አንዱ ነው ፍሊጶስ!
የኤርትራ አንበሳ የአሶሳው ንጉስ፣
ተወልዶ ያደገው በውጊያ ቁርቁስ፣
ሃብት እንዳካበተ እንዳመለከ ቁስ፣
ስሙን ለማጠልሸት ማነው ሚያለቃቅስ?
ይልቅስ ይልቅስ ይልቅስ ይልቅስ፣
ጉድፎቻችሁን አጥሩ ያላንዳች መቅለስለስ፣
ይቺ ኣጭር ግጥም ነች የኤርትራችን መልስ።
ኤርትራ እንደሆነች ልጆቿን ታውቃለች፣
ሃገሬ እንደሆነች ሸረኛን ታውቃለች፣
ለዛም ነው መንና ዓለምን የተወች፣
አባሃኒ ደንደን ቢዘን የሰፈረች፣
ጠቀራና ሶይራ አዳል የመሸገች።
ብዙነው ዓይነቱ ሰው ሲባል ጀነራል፣
የፍሊጶስ ግና እጂጉን ይለያል፣
ለኤርትራ ሲባል መች ህይወቱን ሳስቷል፣
የኤርትራን ጠላቶች ባይኖቹ ያደባያል፣
የኤርትራ ህዝብም ከሱ ጋር ዘብ ቆሟል፣
ግራም ነፈሰ ቀኝ ጁንታ ይቀበራል፣
ትናንት ዛሬም ነገም እውነት ያሸንፋል።
የኤርትራ ደጀን ያባሃኒ መንፈስ፣
የኤርትራ ግርማ የአዳሉ መንፈስ፣
የኤርትራ ምሽግ የደንደኑ መንፈስ፣
የኤርትራ ዋልታ የቢዘኑ መንፈስ፣
ያገሬን ጠላቶች ሚደመስስ፣
ያገሬን ልጆች ልብ፡ ሚያረሰርስ፣
ማነው የምትሉ፡ አንዱ ነው ፍሊጶስ!
የኤርትራ አንበሳ የአሶሳው ንጉስ፣
ተወልዶ ያደገው በውጊያ ቁርቁስ፣
ሃብት እንዳካበተ እንዳመለከ ቁስ፣
ስሙን ለማጠልሸት ማነው ሚያለቃቅስ?
ይልቅስ ይልቅስ ይልቅስ ይልቅስ፣
ጉድፎቻችሁን አጥሩ ያላንዳች መቅለስለስ፣
ይቺ ኣጭር ግጥም ነች የኤርትራችን መልስ።
ኤርትራ እንደሆነች ልጆቿን ታውቃለች፣
ሃገሬ እንደሆነች ሸረኛን ታውቃለች፣
ለዛም ነው መንና ዓለምን የተወች፣
አባሃኒ ደንደን ቢዘን የሰፈረች፣
ጠቀራና ሶይራ አዳል የመሸገች።
ብዙነው ዓይነቱ ሰው ሲባል ጀነራል፣
የፍሊጶስ ግና እጂጉን ይለያል፣
ለኤርትራ ሲባል መች ህይወቱን ሳስቷል፣
የኤርትራን ጠላቶች ባይኖቹ ያደባያል፣
የኤርትራ ህዝብም ከሱ ጋር ዘብ ቆሟል፣
ግራም ነፈሰ ቀኝ ጁንታ ይቀበራል፣
ትናንት ዛሬም ነገም እውነት ያሸንፋል።