Page 1 of 1

የቢዘኑ መንፈስ . . . [ሰሞንኛው ግርድፍ ኤርትራዊ ግጥም]

Posted: 25 Aug 2021, 02:57
by Meleket
የቢዘኑ መንፈስ [ሰሞንኛው ግርድፍ ኤርትራዊ ግጥም]

የኤርትራ ደጀን ያባሃኒ መንፈስ፣
የኤርትራ ግርማ የአዳሉ መንፈስ፣
የኤርትራ ምሽግ የደንደኑ መንፈስ፣
የኤርትራ ዋልታ የቢዘኑ መንፈስ፣
ያገሬን ጠላቶች ሚደመስስ፣
ያገሬን ልጆች ልብ፡ ሚያረሰርስ፣
ማነው የምትሉ፡ አንዱ ነው ፍሊጶስ! :mrgreen:

የኤርትራ አንበሳ የአሶሳው ንጉስ፣
ተወልዶ ያደገው በውጊያ ቁርቁስ፣
ሃብት እንዳካበተ እንዳመለከ ቁስ፣
ስሙን ለማጠልሸት ማነው ሚያለቃቅስ? :lol:
ይልቅስ ይልቅስ ይልቅስ ይልቅስ፣
ጉድፎቻችሁን አጥሩ ያላንዳች መቅለስለስ፣

ይቺ ኣጭር ግጥም ነች የኤርትራችን መልስ። :lol:

ኤርትራ እንደሆነች ልጆቿን ታውቃለች፣
ሃገሬ እንደሆነች ሸረኛን ታውቃለች፣
ለዛም ነው መንና ዓለምን የተወች፣
አባሃኒ ደንደን ቢዘን የሰፈረች፣
ጠቀራና ሶይራ አዳል የመሸገች። :mrgreen:

ብዙነው ዓይነቱ ሰው ሲባል ጀነራል፣
የፍሊጶስ ግና እጂጉን ይለያል፣
ለኤርትራ ሲባል መች ህይወቱን ሳስቷል፣
የኤርትራን ጠላቶች ባይኖቹ ያደባያል፣
:mrgreen:
የኤርትራ ህዝብም ከሱ ጋር ዘብ ቆሟል፣
ግራም ነፈሰ ቀኝ ጁንታ ይቀበራል፣
ትናንት ዛሬም ነገም እውነት ያሸንፋል።
:mrgreen:

Re: የቢዘኑ መንፈስ . . . [ሰሞንኛው ግርድፍ ኤርትራዊ ግጥም]

Posted: 27 Aug 2021, 09:35
by Meleket
ሃገሬ ኤርትራ ልትኮሪ ይገባሻል፣
ዓለም አናጋሪ ጀነራል ወልደሻል። :mrgreen:

ጠላትሽን ሁሉ ዘርሮ ሚያደባይ፣
ፍሊጶሰ-ቢዘን የሃገሩ አገልጋይ። :lol:

ጦርነት ሳይንስ ነው ቢባልም አስሬ፣
ይልቅስ ጥበብ ነው በኤርትራ አገሬ፣

አናምንም ካላችሁ ይሀው ምስክሬ፣
ወራሪን ዘራሪ የጦሩ ገበሬ፣
ጥንቁቁ ጀነራል ፊሊጶስ ‘ኣጅሬ’!
:mrgreen: