ወደ ግንባር ከአዲስ አበባ ሽኝት የተደረገልን 11 ቅጥቅጥ መኪና ውስጥ በአንዱ መኪና ውስጥ ቢያንስ 45 ወንዶችና ጥቂት ሴቶች ነበርን አመሻሽ ላይ ስለወጣን ደብረ ብርሀን ማደር ግድ ሆነብን ለሸገር ልጅ ማታ የነበረው ደማቅ አቀባበልና ግብዣ ልዩ ነበር፤ ለሊት ዘጠኝ ሰአት ለጉዞ እንድንዘጋጅ ተነግሮን ወደ ወረዳ አዳራሾች ተበታትነን አረፍን።
የሚያስደነግጠው ነገር በለሊት ተከሰተ በየመኪኖቹ ተሳፍሮ ከነበረው ዉስጥ የቀረ ከአስር ሰው አይቀርም እኔ የተሳፈርኩበት ውስጥም ከሹፌሩ ጋር 7 ነን ደነገጥኩኝ ምን ይባላል ፍርሀት ያዘኝ እንዲያስተባብሩ የተመደቡ ወደ 12 አስተባባሪዎች ውስጥም 4 ነው የቀሩት፤ ሁላችንም ግራ ተጋባን።
ከዛ አስተባባሪዎች አሸጋሽገው በሁለት መኪናና በአንድ አስተባባሪ አርገው ሸኙን።
እንዲያተርፈኝ አምላኬን እማጸናለሁ
በስሜት የሄድኩ የሸገር ልጅ
Saron Aredo
Please wait, video is loading...