ሽማግሌው (ጎቤ?) "አምስት ሚልየን አማራ ለ አምስት ሚልየን ትግሬ ብንመድብ እንኳን እነሱ ያልቃሉ እኛ የተቀረነው ነፃ እንወጣለን" ነበር ያለው።
አቶ አገኘውም ሙሉ የትግራይ ህዝብን በጠላትነት በመፈረጅ የታጠቀን(ትጥቁ አልተገለፀም) ሁሉ የትግራይ ህዝብ ላይ በማዝመት (human wave በመልቀቅ) ከምድረ ገፅ እናጠፋዋለን ነው መልክቱ ። የአማራ ክልል ኢሊት የፈደራል መዋቅሩንም ስለተቆጣጠረ ሌሎችንም ክልሎች በዘር ማጥፋቱ ጦርነት እናሳትፋለን ነው ስሌቱ።
ይህ ግልፅ የዘር ማጥፋት ጥሪ ነው። የህዝብ ለህዝብ ዕልቂት ጥሪ ነው። በተለይ በሃገሪቱ የምትኖሩ "ማይኖሪቲዎች" ይህን ነገር ነገ በኔ ማለት ይገባችዋል።
የትግራይ ህዝብ ቁጥር አንስተኛ ነውና እናጠፋዋለን የሚል ስሌት በዚህ ዘመን አይሰራም። ኢትዮዽያዉያን ዝም ቢሉ ሌላው አለም ዝም አይልም። ይህን አደገኛ አካሄድ መቃወም የግድ ነው።
Please wait, video is loading...