============================
እጅግ የተወደዳችሁና የተከበራችሁ #የወልድያ_ከተማና_አካባቢዋ ነዋሪወች በሙሉ‼
በራያ ግንባር ላይ አሁን ባለው ወቅታዊ የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ #የነዋሪውን_ደህንነት_ለማስጠበቅ ሲባል ከሃምሌ 12 ቀን 2013 ዓ•ም ጀምሮ #ከምሽቱ 2:00 በኃላ በከተማችን የትኛውም አይነት ተሸከርካሪና የሰው እንቅስቃሴ እንደማይኖር #የሰአት_ገደብ የግንባሩ ኮማንድ ፖስት ያስተላለፈ መሆኑን እናሳውቃለን።
ስለሆነም የሰአት ገደቡ #እንዲከበርና_ለህልውና_ዘመቻው ምቹ ሁኔታ በመፍጠር በኩል መላው የከተማችን ነዋሪ #የነቃ_ተሳትፎ እንዲኖራችሁ አበክረን እንጠይቃለን።
ነገር ግን ይህንን የሰአት ገደብ #ተላልፎ_በሚገኝ_አካል ላይ የግንባሩ ኮማንድ ፖስት ተገቢውን ርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ከወዲሁ እናስገነዝባለን።
Please wait, video is loading...