Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 10186
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

በትግራይ ከተሞች ተጥሎ የነበረው የሰአት እላፊ ከተሰረዘ በኃላ፤ በወልድያ ከተማ (120km ከደሴ) ኣዲስ የሰአት እላፊ ገደብ ተጣለ! ጦርነቱ ወዴት ወዴት ነው የሚሄደው?

Post by sarcasm » 19 Jul 2021, 18:45

#የሰአት_እላፊ_ገደብ_በወልድያ_ከተማ‼
============================
እጅግ የተወደዳችሁና የተከበራችሁ #የወልድያ_ከተማና_አካባቢዋ ነዋሪወች በሙሉ‼

በራያ ግንባር ላይ አሁን ባለው ወቅታዊ የሰላምና ፀጥታ ሁኔታ ጋር በተያያዘ #የነዋሪውን_ደህንነት_ለማስጠበቅ ሲባል ከሃምሌ 12 ቀን 2013 ዓ•ም ጀምሮ #ከምሽቱ 2:00 በኃላ በከተማችን የትኛውም አይነት ተሸከርካሪና የሰው እንቅስቃሴ እንደማይኖር #የሰአት_ገደብ የግንባሩ ኮማንድ ፖስት ያስተላለፈ መሆኑን እናሳውቃለን።

ስለሆነም የሰአት ገደቡ #እንዲከበርና_ለህልውና_ዘመቻው ምቹ ሁኔታ በመፍጠር በኩል መላው የከተማችን ነዋሪ #የነቃ_ተሳትፎ እንዲኖራችሁ አበክረን እንጠይቃለን።

ነገር ግን ይህንን የሰአት ገደብ #ተላልፎ_በሚገኝ_አካል ላይ የግንባሩ ኮማንድ ፖስት ተገቢውን ርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ከወዲሁ እናስገነዝባለን።
Please wait, video is loading...