ሙፈሪያት ከሚል የስልጤ ንግሥት ተባለች !!
Posted: 11 Jun 2021, 01:41
የዛሬ ሁለት ቀን የስልጤ ማህበረ ሰብ ሙፈሪያ ከሚልን የጊሥትነት ማዕረግ ሾሞዋታል! ደስ የሚለ ነው! ይገባታል!! እንኳን ደስ ያለሽ እላለሁ !!
ይህን ሃረግ የከፈትኩት ይህ ሹመት (ማዕረግ) የመላ ጉራጌ ታሪካዊ ባህል መሆኑና ትክክለኛ ትርጉሞቹን ለማያውቁ መረጃ እንዲሆን ብዬ ነው ። በቅድሚያ ሌላ ንትርክ ውስጥ ለመግባት ሳይሆን ስልጤ በግንዱም ሆነ በባህሉ፣ በታሪኩም ሆነ በሳይኮሎጂው ጉራጌ መሆኑን የጉራጌ አንዱ ጎሳ መሆኑን መጥቀስ እውዳለሁ ።
ጊሥቴ ምንድን ነው? ምን ማለት ነው? በጉራጌ ባህል ውስጥ ዛሬ አጠቃቀሙ እንዴት ነው?
ጊሥት ወይም ጊሥቴ ማለት በጥሬ ትርጉሙ ንግሥት ማለት ነው ። ቃሉ በመላ የኢትዮጵያ ሴም ቋንቋ ያለ ሲሆን ጋዝ፣ አጋዝ፣ ገዥ፣ ነጋሲ፣ ንጉሥ፣ ንግሥት ማለት ነው። በታሪክ ብዙ የጉራጌ ጎሳዎች ክስታኔን፣ ስልጤን ጨምሮ ሴቶችን ያነግሱ ነበር ። በጉራጌኛ ጋስ ማለት ጦርነት፣ ዘመቻ ማለት ሲሆን አጋስ፣ አጋሲ፣ ኣጋዝ ጦር አዛዥ ማለት ነው ። የጦር ጌታ አበጋዝ (አባ ጋዝ) ይባላል። ያው ድሮ የጦር አዛዥ ንጉሱ ነበር። ይህ የንጉስና የጦር ጌታ ወደ ሴቶቹ (እንሺታተ) ሲመጣ ጊሥቴ ይባላሉ ።
አሁን የነጋሲ ሴራ በሌለበት ዘመን ይህ የክብር ስም ለታላላቅ ሰዎች፣ ያገር አባት ለሆኑ መሪዎች የክብር ስም ነው ። በቤተሰብ ደረጃ እጅግ ባሊቅ የሆኑት ለምሳሌ አንጋፋ አያት አጋ ሲባል ሴት አያት ደሞ ጊስቴ ብለን እነቆላምጣቸዋለን፣ ጌቶች፣ እሜቴ፣ ንግስቴ፣ ክብርት እንደ ማለት ነው ።
በጉራጌ ወጣቶች ዘንድ በተለይ በክስታኔዎች ዘንድ ልጃገረድ ጓደኞች በክብር እርስ በርስ ሲቆላመጡ በስማቸው አይጠራሩም፤ ዬጎስቴ ተባብለው ነው የሚጣሩት ። ወንድ ጎረምሶች አጉሽት ይባላሉ ። የቃሉ ስር ያው ጋስ ጎሽ፣ ጉሽት፣ አጉሽት ጉሽቴ፣ ጊስቴ የሚለው ነው።
ስለሆነም ጊስቴ የሚለው የንግስትነት፣ የመሪነት ማዕረግ ለክብርት ሙፈሪያት ከሚል ይገባታል ። ባህሉ ግን የመላ ጉራጌ ባህል ነው። ያው እንደ ሚባለው ስልጤ ከጉራጌ ተለየ እንጂ ባህልና ታሪኩ ጉራጌ ነው ።
ሆረስ ዐይነ ኩሉ ዘአማውቴ
ይህን ሃረግ የከፈትኩት ይህ ሹመት (ማዕረግ) የመላ ጉራጌ ታሪካዊ ባህል መሆኑና ትክክለኛ ትርጉሞቹን ለማያውቁ መረጃ እንዲሆን ብዬ ነው ። በቅድሚያ ሌላ ንትርክ ውስጥ ለመግባት ሳይሆን ስልጤ በግንዱም ሆነ በባህሉ፣ በታሪኩም ሆነ በሳይኮሎጂው ጉራጌ መሆኑን የጉራጌ አንዱ ጎሳ መሆኑን መጥቀስ እውዳለሁ ።
ጊሥቴ ምንድን ነው? ምን ማለት ነው? በጉራጌ ባህል ውስጥ ዛሬ አጠቃቀሙ እንዴት ነው?
ጊሥት ወይም ጊሥቴ ማለት በጥሬ ትርጉሙ ንግሥት ማለት ነው ። ቃሉ በመላ የኢትዮጵያ ሴም ቋንቋ ያለ ሲሆን ጋዝ፣ አጋዝ፣ ገዥ፣ ነጋሲ፣ ንጉሥ፣ ንግሥት ማለት ነው። በታሪክ ብዙ የጉራጌ ጎሳዎች ክስታኔን፣ ስልጤን ጨምሮ ሴቶችን ያነግሱ ነበር ። በጉራጌኛ ጋስ ማለት ጦርነት፣ ዘመቻ ማለት ሲሆን አጋስ፣ አጋሲ፣ ኣጋዝ ጦር አዛዥ ማለት ነው ። የጦር ጌታ አበጋዝ (አባ ጋዝ) ይባላል። ያው ድሮ የጦር አዛዥ ንጉሱ ነበር። ይህ የንጉስና የጦር ጌታ ወደ ሴቶቹ (እንሺታተ) ሲመጣ ጊሥቴ ይባላሉ ።
አሁን የነጋሲ ሴራ በሌለበት ዘመን ይህ የክብር ስም ለታላላቅ ሰዎች፣ ያገር አባት ለሆኑ መሪዎች የክብር ስም ነው ። በቤተሰብ ደረጃ እጅግ ባሊቅ የሆኑት ለምሳሌ አንጋፋ አያት አጋ ሲባል ሴት አያት ደሞ ጊስቴ ብለን እነቆላምጣቸዋለን፣ ጌቶች፣ እሜቴ፣ ንግስቴ፣ ክብርት እንደ ማለት ነው ።
በጉራጌ ወጣቶች ዘንድ በተለይ በክስታኔዎች ዘንድ ልጃገረድ ጓደኞች በክብር እርስ በርስ ሲቆላመጡ በስማቸው አይጠራሩም፤ ዬጎስቴ ተባብለው ነው የሚጣሩት ። ወንድ ጎረምሶች አጉሽት ይባላሉ ። የቃሉ ስር ያው ጋስ ጎሽ፣ ጉሽት፣ አጉሽት ጉሽቴ፣ ጊስቴ የሚለው ነው።
ስለሆነም ጊስቴ የሚለው የንግስትነት፣ የመሪነት ማዕረግ ለክብርት ሙፈሪያት ከሚል ይገባታል ። ባህሉ ግን የመላ ጉራጌ ባህል ነው። ያው እንደ ሚባለው ስልጤ ከጉራጌ ተለየ እንጂ ባህልና ታሪኩ ጉራጌ ነው ።
ሆረስ ዐይነ ኩሉ ዘአማውቴ