Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Abdisa
Member+
Posts: 5754
Joined: 25 Apr 2010, 19:14

“የሰሜን ዕዝን ላይ በ45 ደቂቃ ውስጥ መብረቃዊ ጥቃት በመፈጸም ከጥቅም ውጭ አድርገናዋል” - ሴኩቱሬ ጌታቸው

Post by Abdisa » 11 May 2021, 22:50



ዋሺንግተን ዲሲ —

የሕወሓት የቀድሞ አመራር አባል ሴኩቱሬ ጌታቸውን ጨምሮ አራት አመራሮች መገደላቸውን መንግሥት አስታወቀ። ከአንድ ወር በፊት በድምፀ ወያኔ የቴሌቭዥን ጣቢያ ላይ በነበራቸው ውይይት “የሰሜን ዕዝን ላይ በ45 ደቂቃ ውስጥ መብረቃዊ ጥቃት በመፈጸም ከጥቅም ውጭ አድርገናዋል” ሲሉ የተናገሩት አቶ ሴኩቱሬ ጌታቸውን ጨምሮ አራት ከፍተኛ የሕወሃት አመራሮች ከነአጃቢዎቻቸውና ጠባቂዎቻቸው ሲደመሰሱ ዘጠኝ ደግሞ በቁጥጥር ስር ዋሉ ሲሉ የመከላከያ ሰራዊት ሃይል ስምሪት መምሪያ ኃላፊ ብርጋዴል ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በሰጡት መግለጫ አስታወቁ።

የጀኔራል ተስፋዬ አያሌውን ቃል ጠቅሶ ኢዜአ ማምሻውን በሰበር ዜና እንደዘገበው ከአቶ ሴኩቱሬ ጌታቸው በተጨማሪ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ሥራ አስኪያጅና የብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ዘርአይ አስገዶምን ጨምሮ በርካቶች ተደምስሰዋል ብሏል።

በተጨማሪም የድምጸ ወያኔ ሃላፊ የነበሩት አቶ አበበ ገብረመድህን እንዲሁም አቶ ዳንኤል አሰፋ የተባሉ የክልሉ ፋይናንስ ቢሮ ሃላፊ የነበረ ከሹፌሮቻቸውና ከጥበቃዎቻቸው ጋር በመከላከያ ሠራዊት፣ በፌደራል የጸጥታ ተቋማትና በትግራይ ሕዝብና በክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር በተደረገ የተቀናጀ ዘመቻ መደምሰሳቸውን ብርጋዴል ጀኔራል ተስፋዬ አያሌው ለኢዜአ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል የትግራይ ክልል አፈ ጉባኤ የነበሩት ወይዘሮ ቅዱሳን ነጋ እና የቀድሞ የትግራይ ክልል ከተማ ልማት ቢሮ ሃላፊና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ የነበሩ ዶክተር ሰለሞን ኪዳኔ፣

የማረት ስራ አስፈጻሚ የነበሩት አቶ ተክለወይኒ አሰፋ፣ የክልሉ ንግድ ቢሮ ሃላፊ የነበሩት አቶ ገብረመድህን ተወልደ፣ የክልሉ መንገድ ትራንስፖርት ቢሮ ሃላፊ የነበሩት አቶ ወልደጊዮርጊስ ደስታ፣በሱዳን የኢትዮጵያ የቀድሞ አምባሳደር የነበሩት አምባሳደር አባዲ ዘሙ የመለስ አመራር አካዳሚ ፕሬዚዳንትና የኢፈርት ቦርድ ሃላፊ የነበሩት አቶ ቴዎድሮስ ሃጎስ፣ የክልሉ ምክር ቤት ህግ አማካሪ የነበሩት ወይዘሮ ምህረት ተክላይ እና

የክልሉ የንብረትና ግዢ ሥራ ሂደት ሃላፊ የነበሩት አቶ ብርሃነ አደም መሃመድ ሁሉም በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጄብርጋዴል ጀኔራሉ ገልጸዋል።

sesame
Member+
Posts: 5882
Joined: 28 Feb 2013, 17:55

Re: “የሰሜን ዕዝን ላይ በ45 ደቂቃ ውስጥ መብረቃዊ ጥቃት በመፈጸም ከጥቅም ውጭ አድርገናዋል” - ሴኩቱሬ ጌታቸው

Post by sesame » 12 May 2021, 01:02

By explicitly describing in detail what, how and why the TPLF started the war, this guy has done Ethiopia a great favour. All agame efforts to deny that they started the war is null and void as he boastfully declares that the TPLF demobilized (I think he means immobilize) the Northern Command and confiscate their military arsenal. I have been trying to find what Debretsion was saying before the tide turned against the TPLF but I couldn't find them in youtube. I think agames have deleted the official videos released by Tigray TV and DW. But I am sure that they are available somewhere. So would you please anyone post Debretsion's speeches in the first week of the war.

Abdisa
Member+
Posts: 5754
Joined: 25 Apr 2010, 19:14

Re: “የሰሜን ዕዝን ላይ በ45 ደቂቃ ውስጥ መብረቃዊ ጥቃት በመፈጸም ከጥቅም ውጭ አድርገናዋል” - ሴኩቱሬ ጌታቸው

Post by Abdisa » 12 May 2021, 01:25

Had the Tigray terrorists succeeded in causing further damage to the Ethiopian Defense Forces and destabilized the country, their tone today would have changed to what Sekurte Getachew said in the video -- admit, acknowledge, confess and boast about their preemptive strike on the Northern Command Forces. But they're hardwired to deny their own public statements that don't fit their current predicament, pretty much what their cadre eden/Sarcasm has been doing here ad nauseam.


Abdisa
Member+
Posts: 5754
Joined: 25 Apr 2010, 19:14

Re: “የሰሜን ዕዝን ላይ በ45 ደቂቃ ውስጥ መብረቃዊ ጥቃት በመፈጸም ከጥቅም ውጭ አድርገናዋል” - ሴኩቱሬ ጌታቸው

Post by Abdisa » 12 May 2021, 23:05

Aba Awash wrote:
06 Nov 2020, 13:40
Our TPLF forces preemptively disabled the Northern Command and confiscated all military hardware. I wonder where they're heading next.
viewtopic.php?f=2&t=235755
:evil: :evil: :evil:

Post Reply