Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Zmeselo
Senior Member+
Posts: 33606
Joined: 30 Jul 2010, 20:43

እብዷ ሃኪም!

Post by Zmeselo » 11 May 2021, 11:03

ኤርትራውያን ለነጻነታቸው የከፈሉት መስዎእትነት፡ በቃላት ለመግለጽ የሚከብድ ነው። ከባህር በጭልፋ፡ ለኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችን እናካፍላችሁ። @dejene_2011




POLITICS/አማርኛ
እብዷ ሃኪም!

By Meadi Guasot

https://shidamedia.com/%e1%8a%a5%e1%89% ... %e1%88%9d/

May 11, 2021



ሚኒ ስከርቷን ሊነካ የሚንደረደረው ሃር መሳይ ረጂም ጠጉሯን እያማታች፡ በትምህርትና በማህበራዊ ኑሮዋ የደመቀ ህይወት የነበራት ሃኪም፡ የደረሰችበትን ጥግ ማን ይገምተዋል? የደም ገንቦ የሆነችው ይህች አማላይ ወጣት፡ እድሏ ሰውን የሚታዘቡ እንደሚመስሉት ውብ አይኖቿ ሁሉ ያማረ ነበር፡፡

ለከፍተኛ ትምህርት የነጻ ትምህርት ያገኘቸው፡ ቤላሩስ ነበር፡፡ ትምህርቷን በሚገባ አጠናቃ በጥርስ ህክምና ዶክተር ሆና የተመለሰችው ወጣቷ ምሁር፡ እስከዚህ የህይወቷ ምእራፍ ድረስ ሙሉ ጤናማ ነበረች፡፡ እብደቷ የጀማመራት፡ የፈረስ ጭራ የሚመስለውን ጠጉሯን ቆርጣ አፍሮ የሆነች እለት ሳይሆን አይቀርም! ማን ያቃል፡ መቀሱን ተመስሎ የገባ መንፈስ ቢኖርስ?

ብቻ ከፍተኛ ደሞዝ ከምትከፈልበት ከፍተኛ ሞያና፡ ሊያገቧት ደጇን ከሚጠኑ የዘመኑ ዘናጭ ጉብሎች ኮብልላ፡ ሳህል ተገኘች፡፡ ይህች በዴንቲስትነት የተመረቀችው ወጣት፡ እብደቷ እየባሰባት መትቶ፡ በቦንብ የፈረሰ ፊት፡ ከሌላ የገላ አካል እየቆረጠች መገጣጠም ጀመረች፡፡ እርግጥ ነው፡ እሷንና ኦሮታ ሆስፒታልን ነጣጥሎ ማየት አይቻልም፡፡

ምንም እንኳን ከሌላው የተሻለ አደጋ የሌለበት ስፍራ ቢሆንም፡ እንደሌሎቹ ማግባትና መውለድ ስትችል፡ 'የያዝኩት ጉዳይ መች አነሰኝ' በማለት ስራዋ ላይ ብቻ አተኮረች፡፡ እርግጥ ነው ውበቷ፤ ልጅነቷ፤ እውቀቷ የማያሳሳት እብዷ ሃኪም፤ እኛ እብድ መሰለችን እንጂ፤ ከጋብቻም ከልጅም ከራሷም በላይ ያየችው ቁምነገር ብዙ ቮልዩም የሚፈጁ መጻህፍት የማይበቁት ታሪክ አላት፡፡

የእናት አገር ጥሪ ገጹ ይሞላ ዘንድ፡ ይህች ወጣት ስለዋለችው ውለታ ዝንተ አለማችንን ስናወሳት እንኖራለን፡፡ ዶ/ር ላይነሽ ህይወት የዘራችባቸው ሁሉ፡ ልጆቿ ናቸው፡፡ ሞያዋን ሳትሳሳ ያቀበለቻቸው ሁሉ፡ ልጆቿ ናቸው፡፡ ከ 50 አመታት በላይ ሳትደክም ያገለገለችው የኤርትራ ህዝብ፡ በሙሉ ልጆቿ ናቸው፡፡

ዛሬ የእናቶች ቀን ሲከበር ከዶ/ር ላይነሽ የበለጠ እናት ይገኝ እንደሆነ፡ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ስላፈራሻቸው ልጆችስ በሙሉ፡ ስለአገልግሎትሽም አንቺ ከእናቶች ሁሉ የበለጥሽ እናት ነሽና፡ ፍቅርና ሞገስ ከሙሉ ኤርትራ ህዝብ ይድረስሽ! ተነግሮ ስለማያልቅ ውለታችሁ፡ ለኛ ስትሉ ማህጸናችሁን የዘጋችሁ ሁሉ፡ ታሪክ ሲያከብራችሁ ይኖራል፡፡

እናከብራችኋለን!

እናትም አባትም አገራችን ኤርትራ ለዘላለም ትኑር/ይኑር!

Zmeselo
Senior Member+
Posts: 33606
Joined: 30 Jul 2010, 20:43

Re: እብዷ ሃኪም!

Post by Zmeselo » 11 May 2021, 11:28





Ethiopia is committed to rebuilding Tigray and ensuring that citizens are sufficiently provided for, while rebuilding efforts are being exerted. We welcome the International Community’s support, in efforts to scale up Humanitarian Assistance and close existing gaps.

The following actions have been taken in Tigray: The second round of Humanitarian Assistance has delivered food and other essential items, to 2.7 million people;

Emergency shelters and non-food item kits supplied to over 245,000 displaced persons in Tigray;

The Ministry of Health (@FMoHealth) has been working to operationalize health facilities in the region, with provisions of emergency supplies. Up to 60 Mobile Health teams, have been established;

Humanitarian support has been improved with implementation, of a notification system. Previously inaccessible areas, now being reached with help of military escorts;

Visa extension permits are being granted, to humanitarian groups. New guidelines have been introduced, for permits to use communication equipment;

More than 192 staff members of UN-Agencies, international NGO’s including International Media have been provided access to the region;

The Ministry of Finance (@MoF_Ethiopia) and the Ministry of Peace (@MoP_Ethiopia) are working closely with the EU, the World Bank and the UNDP, in order to rebuild damaged and destroyed economic and social infrastructures;

An Emergency Coordination Center (ECC) has been established in Mekele comprising of relevant Ministries, Regional Bureaus, UN-Agencies, bi-lateral and international NGOs;

The Federal Ministry of Agriculture (@MoA_Ethiopia) has allocated Birr 10 million to strengthen the regional agriculture and natural resource bureaus, with shipment of 14k tons of fertiliser;

The Ministry of Education (@fdremoe), has allocated Birr 95 million for reopening of schools and dispatched 1 million facemasks to the region.


#PMOEthiopia- (Office of the Prime Minister - Ethiopia
@ PMEthiopia)

Post Reply