1 - በአፋር VS ሱማሌ ጦርነት በ1ቀን ከ300 በላይ ወታደሮች ተግደሉ ...
በአፋር እና በሱማሌ መካከል የሚደረገው የሰሞኑ ጦርነት ይህ በፎቶው ላይ የሚታየው የሱማሌ ክልል ልዩ ሃይል ኮሮኔልን ጨምሮ ከ200 በላይ ሠዎችን እየፈጀ ነው። አፋር እና ሱማሌ ይሄንን ያክል በልዩ ፖሊስ ደረጃ የሚያዋጋ ጥላትን እንዴት እንዳመጡት አይገባኝም። የሁለቱ ክሎሎች መሪዎች ቆም ብለው ሊያስቡ ይገባል። እናተን ድንበር ላይ የሚያዋጋው ክልሎችን፣ ልዩ ፖሊሶችን አፍርሶ ሁለታቹንም ወደ ባርነት ሊያስገባቹ ያቀደ አህዳዊ ቡድን ነው። እነ አብይ፣ እነ ተመስገን ጥሩነህ በሴራ የሚያዋጓቹ ለጭቁን ህዝባቹ ነፃነትን ሊያመጡላቹ አይደለም ልትነቁ ይገባል።

ፈጽሞ መንግስት አለ ለማለት አያስደፍርም።
በአሁኑ ሰአት በሁለቱ የአፋር እና የሶማሊ ጎሳ ወገኖቻችን መካከል በተፈጠረው ጦርነት በጥቂት ቀናት ውስጥ ከሁለቱም ወገን በድምር ከ180 በላይ ሰዎች ህይወት አልፏል።
ይህንን ግጭት ለማስቆም ያልቻለ አካል " መንግስት ነኝ" የማለት ሞራሉ ሊኖረው አይገባም።



2 - ከአፋር ጋር እየተዋጋ ያለው ኢሳ [የሱማሌ ጎሳ] ብቻ ሳይሆን ከታላቋ ሱማሌና ከጅቡቲም የመጡ ወታደሮችም ጭመር ነው ...
NEWS: Afar Daily Integration: አፋር ከኢሳ ጋር ብቻ አይደለም እየተዋጋ ያለው



=============================
ከአፋር ጋር እየተዋጋ ያለው ኢሳ ብቻ እንዳልሆነ በተለያየ ጊዜ ለፌደራል መንግስቱም ተናግረናል ነገር ግን የፌደራል መንግስቱ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎናል። የአፋር ህዝብ ሰሞኑን እየተዋጋ ያለው ከሱማሌ (ሞቃዲሾ) ተጭነው በመጡ የተስፋፊነት አባዜ ያለባቸው የአልሸባብ ጋር እንደሆነ እያየን ነው ለዚህም ማረጋገጫ በጦርነቱ ከተገደሉት ውስጥ አንዱ ሲፈተሽ የተገኘበት መታወቂያ ያሳያል። አሁን እኛ ምንፈልገው እና አለም እንዲረዳን ምንፈልገው የአፋር ህዝብ እየተዋጋ ያለው ከአሸባሪው እሳ ጋር ብቻ ሳይሆን ከባዓድ ሀገር አሸባሪዎች ጋር እንደሆነ እንድታውቁልን እንፈልጋለን።
እስኪ በፎቶው ላይ ተመልከቱ የተላቋን ሶማሊያ መከላኪያ፣የጅቡቲ አፋር ድረስ መጥቶ ነው እየተዋጋን ያለው። ይህ መታውቂያ ትላንት በተደመሰሰው የሶማሌ አሸባሪዎች ላይ የተገኘ ማስረጃ ነው !! ለአፋር ህዝብ አንድም የሚጨውለት ሚዲያ ጠፍቶ በማየቴ ግን እኔ ኢትዮጵያዊ አይደለውም እንደል አስገድዶኛል። አሁንም እደግመዋለው እኔ ኢትዮጵያዊ አይደለውም ከዚህ ቦሃላ። የአፋር ህዝብ እንዲህ በበአድ ሀገራት ወራሪዎች ሲወረር ሌላ ጊዜ ስለ ኢትዮጵያ ሚያወሩት ሁሉ ዝም ብለው ስለ ሌላ ታሪክ ያወራሉ። ታዲያ ለአፋር ያልሆነች ኢትዮጵያ ለኔ ምኔ ነች እና ነው እኔ ኢትዮጵያዊ ነኝ ምለው?
የጅግጅጋው ቤተመንግስት ሰባኪ መስጠፋ ኡመር ከትላንት ጀምሮ በአይሱዚ እና በተሳቢ አሳፍሮ ወደ ስፍራው ወጣቶችን ሲልክ እንደ ነበር በቪድዮ ለቅቄ ነበር ነገር ግን ሰሚ አላገኘውም። ዛሬ ላይ የአፋር አርብቶ አደር ምንም በማያውቀው ቤቱ በተቀመጠበት በነዚህ በወራሪ ሀይሎች ይገደላል የሀገራችን ሚዲያዎች፣ ታዋቂ ሰዎች ፣ፕሬዝዳንቷ፣ ጠቅላይ ሚንስተሩ ፣ምክትሉ በአጠቃላይ ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ እያሉ ቀን ቀን ጆሯችንን የሚያደናቁሩን ለአፋር ህዝብ ሲሆን ዝም ማለታቸው አፋር የበለጥ እንዲጠነክር ያደርገዋል እንጂ መቼም አያሰማቀውም።
Afar Daily Integration

