Please wait, video is loading...
Finally and officially ከግዚያዊ የትግራይ ኣስተዳደር የሆነ ኣመራር በግልጽ
√ ህግ ከማስከበር ኣላማ ውጪ ከጎረቤት ሃገር እና ክልል ጦር( የኤርትራ ጦር እና የኣማራ ልዩ ሃይል ማለቱ ነው) ለመግባቱ እና ከባድ ውድመት ለማድረሳቸው ምስክርነት ሰጥታል።
√ ትግራይ ውስጥ ያለው ፋብሪካዎች ሙሉ ለሙሉ መውደሙ እና በ30 ኣመት ሙሉ የተገነባው ሁሉ እንደወደመ እና እንደተዘረፈ በግልጽ ከነ ማሳያወቹ ዘርዝራል። እንደሱ ኣነጋገር "ኣንድ ሳይቀር" መውደሙን ነው ያመነው።
√ የኣክሱም እና የዓዲ ግራት ዩኒቨርስቲም ሙሉ ለሙሉ መውደማቸዋል ኣምናል።
√ የትግራይ መንግስት፣ህዝብ እና ንብረት የሆነ ንብረት በሙሉ እንደተዘረፈ የግል ኮንስትራክሽን ንብረቶች ሳይቀር ከሚሰሩ ህንፃዎች እና ፕሮጆክቶች ጭምር ወደ ጎረቤት ኣገር፣ ኣማራ ክልል እና ወደ ማሃል ኣገር እንደተወሰደ በግልጽ ኣምናል።( ሲሚንቶ ሳይቀር ነው ያለው)
√ የሌላ ኣገር ወታደሮች ብቻ ሳይሆኑ መከላክያውም ጭምር "ህግ የማስከበር" ጉዳይ ወደ ጎን በመተው ጦርነቱ ላይ ተሳትፎ ነበራቸው በሚል የትግራይ መንግስት እና ህዝብ ንብረት የሆኑት ብዙ መኪናዎች እና ንብረት ወርሰናችዋል በሚል መውሰዱ ይገልፃል።
እስካሁን እየተባለ የነበረው ይህ ነው። እንዲህ ብለው ኣምነው በግልጽ እና በሚድያ መናገራቸው ጥሩ ሁኖ ሳለ በትግራይ ከንብረት መዘረፍ እና መውደም በላይ ብዙ የንፅሃን ሂወት ተቀጥፏል። እናቶቻችን እና እህቶቻችን ተደፍራል። ስንቶች እስካሁን የገቡበት ኣይታወቅም። ይህ በሚያሳዝን መልኩ ኣልተገለፀም። ለንብረት እንጂ ለሂወት እና ለደረሰው የንፅሃን ሂወት መጥፋት ትኩረት ኣልተደረገም። ቢሆንም ይህ ከሚመረው እውነታ በትንሹ ነው።
ቀሰ በቀሰ ሁሉን መውጣቱ ደግሞ ኣይቀሬ ነው!