Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 30914
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

ሆረስና የኢትዮጵያ አጀንዳ፤ ኢትዮጵያ ታንጻ ያላበቃችው የ3 ሺ ዘመን ካቲድራል

Post by Horus » 24 Feb 2021, 01:07

ይህ እኔ ዛሬ ያመጣሁት አዲስ ሃሳብ አይደለም ። የካቲድራል አስተሳሰብ፣ ማለትም በአንድ ትውልድ ተሰርቶ ተፈጥሮ የማያልቅ የረጅም እጅግ የረጅም ዘመን ራዕይና እቅድ ካቲድራላዊ ሃሳብ ይባላል። የኢትዮጵያ አጀንዳ፣ የኢትዮጵያ ሃገረ መንግስት፣ የኢትዮጵያ ስልጣኔ ህንጻ እነጻ፣ ግምባታን የሚገልጸው ጽንሰ ነገር፣ ጽንሰ ሃሳብ ካቲድራዊ ህሳቤ ይባላል።

ለምሳሌ ብዙ ግዜ የኢዜማ ምሁራን ስለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ሲያወሩ በካቲድራል ቋንቋ ነው። እኛ የጀመርነው ልጆች፣ የልጅ ልጆቻችን የፈጽሙታል ይላሉ! ያ ነው የካቲድራል አስተሳሰብ የሚባለው።

እኔ እንደ ሆረስ የሚታየኝ የኢትዮጵያ ጉዞ፣ የኢትዮጵያ አጀንዳ፣ የኢትዮጵያ እድገትና ሃያልነት ያን መሰል የካቲድራል ራዕይ ነው !!

ያ ነው የኢትዮጵያ ሳዳ፣ ያገራችን እጣ ፋንታ፣ ያገራችን ወደ ፊት ቁማ ፌት !!

ይህ የኢትዮጵያ አጀንዳ ምንድን ነው?

አንድ፣ ኢትዮጵያ የተዋሃደች፣ የተረጋጋች፣ ጠንካራ ያፍሪካ አንደኛ ወይም ሁለተኛ ሃያል አገር ትሆናለች ።

ሁለት፣ ኢትዮጵያ ዴሞክራሳዊ፣ ነጻ፣ ፍትሃዊ ማህበረ ሰብ ትሆናለች ።

ሶስት፣ ኢትዮጵያዊያን የበለጸጉ፣ ሃብታም፣ የተማሩ፣ ጤናቸው የተጠበቀ ሕዝብ ይሆናሉ። በ2100 አንድ ቢሊዮን ሕዝብ እንሆናለን !!

አራት፣ ኢትዮጵያዊያን በፈጠራ የረቀቀ፣ ክባቢውን ያለማ፣ መንፈሳዊ ካልቸርና ስልጣኔ ይገነባሉ !!!

ይህ ነው የሚሆነው በልጆቻችንና በልጅ ልጆቻችን ዘመን !!!




Horus
Senior Member+
Posts: 30914
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ሆረስና የኢትዮጵያ አጀንዳ፤ ኢትዮጵያ ታንጻ ያላበቃችው የ3 ሺ ዘመን ካቲድራል

Post by Horus » 24 Feb 2021, 01:51

IF YOU WANT TO UNDERSTAND WHAT I MEAN BY THE ETHIOPIAN AGENDA .... LISTEN TO THIS !!!

እኔ በሚቀጥለው 5 አመት ውስጥ እዚህ ለሰፈረው አንዱ አላማ በፈቃደኛነት ለማገልገል ወስኛለሁ !! በቃ !!!



Horus
Senior Member+
Posts: 30914
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ሆረስና የኢትዮጵያ አጀንዳ፤ ኢትዮጵያ ታንጻ ያላበቃችው የ3 ሺ ዘመን ካቲድራል

Post by Horus » 24 Feb 2021, 02:40

TGAA wrote:
24 Feb 2021, 01:59
Wonderfully put , Horus.
TGAA - thank you. አሁን ያቢይ ብልጽግናና ኢዜማ ለኢትዮጵያ ያላቸው ያ10፣ 20፣ 30 አመት ራዕይ እያስተማሩ አጀንዳ ያለው፣ አላማ ያለው ብሩህ ትውልድ ለመፍጠር ከተወዳደሩ ኢትዮጵያ ታሸንፋለች !!

ዳውሮ


Horus
Senior Member+
Posts: 30914
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ሆረስና የኢትዮጵያ አጀንዳ፤ ኢትዮጵያ ታንጻ ያላበቃችው የ3 ሺ ዘመን ካቲድራል

Post by Horus » 24 Feb 2021, 02:53

አፍሪካን ለመምራት ሁሉን ነገር ይዛ ያለች ኢትዮጵያ የነጻ ሕዝብ ምድር ... !!


TesfaNews
Member+
Posts: 6847
Joined: 14 Feb 2020, 22:23
Location: Ras Mesobawian

Re: ሆረስና የኢትዮጵያ አጀንዳ፤ ኢትዮጵያ ታንጻ ያላበቃችው የ3 ሺ ዘመን ካቲድራል

Post by TesfaNews » 24 Feb 2021, 03:03

Horus wrote:
24 Feb 2021, 01:51
IF YOU WANT TO UNDERSTAND WHAT I MEAN BY THE ETHIOPIAN AGENDA .... LISTEN TO THIS !!!

እኔ በሚቀጥለው 5 አመት ውስጥ እዚህ ለሰፈረው አንዱ አላማ በፈቃደኛነት ለማገልገል ወስኛለሁ !! በቃ !!!

ለምን ኢዜማ ከብልፅግና ጋር አልተዋሃደም!!!

Horus
Senior Member+
Posts: 30914
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ሆረስና የኢትዮጵያ አጀንዳ፤ ኢትዮጵያ ታንጻ ያላበቃችው የ3 ሺ ዘመን ካቲድራል

Post by Horus » 24 Feb 2021, 03:26

ተስፋ ኒውስ፣
በእኔ ግምት አንተ የኢትዮጵያን ታሪካን ፖለቲካ በደንብ የምታቅ ይመስለኛል ። ኢዜማና ብልጽግና መዋሃዳቸው ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል ። ሁለቱ ፓርቲዎች መሰረታዊ ፍልስፍናቸው ይለያያል ። ለምሳሌ ያቢይን ራዕይ ተመልከት ። አንድ አገር የሚበለጽገው፣ አንድ ስልጣኔ የፈጠረው በሰው ግለሰቦች ሃይልና ጥረት፣ ፈጠራና ትግል ነው ብሎ አያውቅም። ብልጽግና የቡድን የጎሳ ኮንሴፕት ላይ የቆመ ሃሳብና ፓርቲ ነው። ኢዜማ ምንም እንኳ ወደ ሶሺያ ዴሞክራሲ ቢያጋድል፣ ታሪክ የሚሰሩት የሚጥሩና የሚፈጥሩ ግለሰቦች ናቸው ብሎ የሚያምን ፓርቲ ነው ። ኢትዮጵያ ከጎሳ ህሳቤ እስከ ምትወጣ ብልጽግና ይኖራል። እድገት እየመጣ ሲሄድ ከበርቴው የጎሳ ክልልና እስር ቤት ሲጠበው ብልጽኛን አፍርሶ ወደ ዜጋነት ሃሳብ ይዞራል፣ ጥቅሙ ስለሆነ !! ዛሬ ግ ን ይህን ደረጃ ማለፍ አለብን ! አቢይ ኢትዮጵያዊነትን ከጎሳነት ጋር ማጣጣም እስከ ሞከረ ድረስ በፖለቲካው አለም ዋጋ ይኖረዋል ። ልብ በል ዎያኔ እንደ ጤዛ የረገፈው ይህን ቁልፍ እውቀት ስላጣ ነው። አንድ ትልቅ አገር በጠብ፣ በክፍፍል፣ በዘረኘት ለረጅም ግዜ መግዛት አትችልም ! ያ ነበር የዎያኔ መጥፊያ ድንቁርና !! አቢይ ያ ገብቶታል ። ግን ገና ያልገባው ነገር ታሪክን የሚፈጥሩት የሆኑ የጎሳ ጥርቅሞች ሳይሆኑ ሌት ተቀን የሚሰሩ፣ የሚለፉ፣ የሚፈጥሩ ግለሰቦች፣ የሰው ልጆች እንጂ የሆኑ የጎሳ ቡድኖች አለመሆናቸው ገና አለገባውም ። ያ ነው የሁለቱ ፓርቲዎች አንድ አለመሆን ምክንያት !! ኬር

Horus
Senior Member+
Posts: 30914
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: ሆረስና የኢትዮጵያ አጀንዳ፤ ኢትዮጵያ ታንጻ ያላበቃችው የ3 ሺ ዘመን ካቲድራል

Post by Horus » 24 Feb 2021, 04:36

አገር የሚኖረው ነጋ ጠባ የሚያለቅሱ ላቅመ አዳም ያልደረሱ ጎሳዎች ስላሉዋት አይደለም ! ባላገር አገር የኔ የሚሉ ሰዎች ስላሉዋት ነው !!

Post Reply