Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
sarcasm
Senior Member
Posts: 10186
Joined: 23 Feb 2013, 20:08

"ባለቤቴ ጫካ ውስጥ መንታ ተገላግላ አረፈች" የትግራዩ ተፈናቃይ በሱዳን (BBC)

Post by sarcasm » 25 Jan 2021, 16:27


የአብርሃ መንታ ልጆች


በትግራይ ክልል ባለው ግጭት ምክንያት በቤቷ ልጆቿን መገላገል ያልቻለችው ነፍሰ ጡር፤ ግጭቱን ሽሽት በጫካ ውስጥ ተደብቃ ሳለ መንታ ልጆቿን ብትገላገልም፤ በህይወት የቆየችው ለጥቂት ቀናት ብቻ ነበር።

እናቲቱ ይህችን አለም ላታያት ለመጨረሻ ጊዜ መሰናበቷን ባለቤቷ ይናገራል።

ልጆቿን ማየት የቻለችው ለአስር ቀናት ብቻ ነበር። ባለቤቷም ልጆቹን በቅርጫት አድርጎ የእርሱ እና የልጆቹን ነፍስ ለማዳን ወደ ጎረቤት አገር ሱዳን ተሰደደ።

ከመንታ ጨቅላዎቹ በተጨማሪ፣ የአምስት ዓመት ወንድ ልጁን፣ የ14 ዓመቱን የባለቤቱን ወንድም ይዞ ሱዳን ገብቷል፤ በአሁኑ ወቅት በስደተኞች መጠለያ ካምፕ ውስጥ ይገኛል። መንታ ህፃናቱን አንዲት አሜሪካዊት ዶክተር ለመርዳት እየሞከረች ነው።


በትግራይ ክልል የተቀሰቀሰው ግጭት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ነዋሪን አፈናቅሏል። 60 ሺህ የሚሆኑት ጨርቄን፣ ማቄን ሳይሉ ወደ ሱዳን ሸሽተዋል።

continue reading https://www.bbc.com/amharic/55789371