Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

ኪዳነ ሓኪምና ታካሚዎቹ - ካልተነገሩት መራር ታሪኮች በጭልፋ

Post by Meleket » 23 Dec 2020, 05:02

ጃንሆይና ደርግ ካልተነገሩት መራር ታሪኮች (ገጽ 171-174)

“ማይሑጻ በተባለው አካባቢ ወንበዴዎች ታይተዋል” የሚል መረጃ የደረሳቸው ወታደሮች ከደቀምሓረ በሶስት ካሚዮን ተጭነው ወደ ማይዕዳጋ ገሰገሱ። እንደደረሱም መኪናቸውን አቁመው በእግር ወደ ውስጥ ገቡ። አደይ ግደይ “ጦር ሰራዊት መጡብን!” ስትል በህክምና ስራው ላይ ለነበረው ባሏ ነገረችው።

ጀብሃ እዚያች መንደር ገብቶ ማደሩን ኪዳነ ሃኪም ሰምቶ ነበር። እና ወታደሮች ለምን እንደመጡ መገመት አልተቸገረም። ስለዚህ ተጣድፎ ባለቤቱንና ልጆቹን አንድ ክፍል ውስጥ ዘግቶባቸው ሲያበቃ እሱ ወደ ህክምና ክፍሉ ተመለሰ። በዚያው ቅጽበት ጥቂት ወታደሮች ወደ ህክምና ጣቢያው እየተንጋጉ ገቡ።

“ ‘ወንበዴዎችን እያከምክ ነው። መድሃኒትም ሰጥተሃቸዋል’ የሚል መረጃ ደርሶን ነው የመጣነው።” ሲሉ አምባረቁበት።

ኪዳነ ሃኪም ረጋ ብሎ፣ “እኔ የመንግስት ወገን እና የመንግስት ሰራተኛ ነኝ። የሚታከሙትንም መመርመር ትችላላችሁ። ገበሬዎች ናቸው።” ሲል ምላሽ ሰጠ።

የተናገረው አልተዋጠላቸውም።

“ደህና! የምትሰራው ሁሉ ወሬው ደርሶናል።” ሲሉ ዛቱበት።

እንዲህ እየተነጋገሩ ሳለ ከማይሑጻ አግጣጫ የቀላል መሳሪያ ተኩስ ተሰማ። በዚህ ጊዜ ሁለቱ ወታደሮች ተሯሩጠው ከህክምና ጣቢያው ወጥተው ሄዱ።

ከጦርሰራዊት ጋር ተቀላቅሎ መረጃ የሚሰጣቸው እንደነበረ ግልጽ ነበር። ይህም ሰው ማይሑጻ ላይ የገረዝግሄር ተኽለንክኤል እረኛ የነበረ የትግራይ ሰው ነበር። ልጆቻቸው ወደ ትግል የገቡ ሰዎችን ስም፣ ታጋዮች መቼ ወደ መንደሪቷ እንደሚመጡ የመሳሰለውን መረጃ ለማቀበል ነበር በእረኛነት የተቀጠረው። ሁዋላ በግልጽ ጠመንጃ ታጥቆ ከጦር ሰራዊቱ ታይቷል።

ወታደሮቹ አመጣጣችው ህዝቡን አስፈራርተው ለመመለስ ይመስል ነበር። ሆኖም የጀብሃ ተዋጊዎች አሸምቀው በመተኮስ ጥቃት ሲሰነዝሩባቸው በርከት ያሉ ወታደሮች ተገደሉባቸው። ከማለዳ የጀመረ ውጊያ እስከ ቀትር ቀጠለ። የጀብሃ የውጊያ ስልት ውጤታማ ነበር። ጥቂት ተታኩሰው ዘወር እያሉ ብዙ አጠቁ። በሌላ አግጣጫ ደግሞ እንዲሁ አደረጉ፤ ሃይላቸውን እየቆጠቡ ከጥቂት በላይ ወታደሮችን ገድለው ተሰወሩ። ወታደሮቹ የወረደባቸውን ሙትና ቁስለኛ ብዛት ሲገነዘቡ እልሃቸውን የሚወጡበት፤ ቁጣቸውን የሚያበርዱበት ማራገፊያ ፈለጉ። ይህም የመንደሪቷ ነዋሪ ሆነ።

ኪዳነ ሃኪም ወታደሮቹ ከሄዱ በሁዋላ ወደ ቤተሰቡ ተመልሶ ከፋፍሎ አልጋ ስር እንዲደበቁ አደረጋቸው። በዚህ ጊዜ ከደጅ “ክፈትልን” የሚሉ ሰዎች ድምጽ ሰማ። ሲከፍት የዑመር አዜንዳ ሶስት ልጆች ነበሩ። አስገባቸውና ከልጆቹ ጋር አልጋው ስር ጨመራቸው። ከዚያም ክፍሏን ቆልፎ ወደ ስራው ተመለሰ።

ህክምናቸውን የጨረሱ ወንዶችና ሴቶች ከልጆቻቸው ጋር በማስተናገጃው ክፍል ተጠቅጥቀዋል። በተኩሱ ምክንያት መንቀሳቀስ ሰግተው ቁጭ ብለዋል። በፍርሃት ተጨባብጠዋል።

ከተማው ውስጥ ተኩስ እየተሰማ ነበር። የታንክ ተኩስ ድምጽ ጭምር የህክምና ጣቢያውን ግድግዳ አነቃነቀው። ከሰአት 2:00 ሰአት አካባቢ ሰባት የሚሆኑ ወታደሮች በቀጥታ ወደ ሆስፒታሉ መጥተው በደም ፍላት መጮኽ ጀመሩ። ጠመንጃቸውን ኪዳነ ሃኪም ላይ ወደሩ፣

“አንተ ጨምላቃ! አሁኑኑ ወንበዴዎችን ለይተህ ስጠን!”

“እዚህ ወንበዴ የለም። እነዚህ የአካባቢው ገበሬዎች ናቸው።”

አንደኛው ወታደር አይኑን አጕረጠረጠ፣

“ከናንተ መካከል ሰላማዊ የሚባል ሰው የለም። ቀንደኛው ወንበዴ ደግሞ አንተው ራስህ ነህ።” ካለው በሁዋላ በአፈሙዝ እየገፋ ከግድግዳ ጋር አስጠጋው። ሌሎች ወታደሮች ደግሞ ወንድና ሴት ታካሚዎችን ለያዩዋቸው። ወንዶቹን በአንድ ክፍል ውስጥ አስገብተው ወደ ግድግዳው በማስጠጋት ደረደሯቸው። ከዚያም እየፈተሹ በኪሳቸው የነበረውን ገንዘብ፤ በእጃቸው ላይ የታሰረውን ሰአት ወሰዱ።
አንድ ሰው ድምጹን ከፍ አድርጎ ተለማመነ፣

“እባካችሁ ተውን! ሰላማዊ ሰዎች ነን። እኔ የቃኘው የአሜሪካ ካምፕ ሰራተኛ ነኝ። ማስረጃ ወረቀት አለኝ። ተመልከቱ።”

“ዝም በል!” የሚል ምላሽ አገኘ።

አንዱ ወታደር የኪዳነ ሃኪምን ጋዋን አወለቀና ፊቱን ሸፍኖ አሰረው። ከዚያም ሌላውን ወታደር፣ “በሳንጃ ውጋው!” ሲል አዘዘው። ኪዳነ ሃኪም በታካሚዎቹ ፊት ደረቱ ላይ በሳንጃ ተወጋ። ከዚያም በእሩምታ ጥይት ጨረሱት። ኪዳነ ሓኪምን የገደለው ወታደር ወደ ደጅ ከወጣ በሁዋላ ጠመንጃቸውን ወድረው በተጠንቀቅ ለቆሙት ወታደሮች ትእዛዝ ሰጠ። የእሩምታ ተኩስ ድምጽ ታካሚዎቹ ላይ ወረደ። እየተደራረቡ ወደቁ። ከዚያም ወታደሮቹ ሴት ታካሚዎች ወደነበሩበት ክፍል ገቡ። ሆኖም አልገደሉም። አዛዣቸው፣ “ጎበዝ እንሂድ” የሚል ድምጽ ሲያሰማ ተመራርተው ወጡ።

ከተማው ውስጥ ብዙ ሰው ገደሉ። የዑመር ሓጭት ሴት ልጅ ውሃ ተሸክማ ስትሄድ ተኩሰው ገደሏት። የአስር አመት ልጅ ነበረች። አደይ ሄዋን ርቃ ከሄደችበት ስትመለስ መንገድ ላይ አገኟት። ዘንቢል ተሸክማ በመንገድ ተዳክማ ነበር። ሃብቶም ተክኤ እና መብራህቶም እንዲሁ ተገድለው ተገኙ። በእረኛነት ተመስሎ መረጃ ሲለቅም የነበረው ሰው ወታደሮቹን እየመራ ሰው አስፈጀ። እረኛው የጠቆመው ሁሉ ያለ ጥያቄ በቅጽበት ተገደለ።

(የህክምና ጣቢያ ውስጥ በጅምላ ከተተኮሰባቸው መካከል ኪዳነ ገረየሱስ የተባለ ሰው ሬሳ ተጭኖት ከሞት ተረፈ። ክፉኛ በመቁሰሉ ግን አንድ እጁ ተቆረጠ። ታሪኩን ለመተክም በቃ። የኪዳነ ሃኪም ልጆች ከሞት አመለጡ። ስምንቱም ልጆቹ፣ ከእናታቸው ጋር ወደ በረሃ በመሄድም ትግሉን ተቀላቀሉ። ልጆቹ በተዋጊ ሰራዊት፣ በከባድ መሳሪያ፣ በህክምና፣ በወታደራዊ ስለላ ክፍሎች ተመድበው ታገሉ። የኪዳነ የመጨረሻ ልጅ ሰናይት የሄሊኮፕተር አብራሪ የሆነች ሲሆን፤ በወያኔ ወረራ ጊዜም በጦርነቱ ተካፍላለች።)

ተራኪዎች ኪዳነ ገሬሱስ፣ ትርሓስ ኪዳነ፣ ሓሊማ ኣድም፡ ዳኒ ዑመር
ማጣቀሻ ፡ ሕድሪ መጽሔት 2008 ቁጥር 37
ጸሓፊ፡ ገነት ስዩም
ኣርታኢና ተርጓሚ፡ ተስፋዬ ገብረኣብ

Sabur
Member
Posts: 1364
Joined: 11 Aug 2018, 07:41

Re: ኪዳነ ሓኪምና ታካሚዎቹ - ካልተነገሩት መራር ታሪኮች በጭልፋ

Post by Sabur » 23 Dec 2020, 07:30


Thank you Meleket !!

Every Village, Every Town, and Every City in Eritrea carries deep scars of The Brutal Atrocities of Innocent Eritreans by the Amhara Led Ethiopian Colonizer Forces.

Eritrea Shall Not forget.

Viva Eritrea !!!

Eritrea for Eritreans !!!


Meleket wrote:
23 Dec 2020, 05:02
ጃንሆይና ደርግ ካልተነገሩት መራር ታሪኮች (ገጽ 171-174)

“ማይሑጻ በተባለው አካባቢ ወንበዴዎች ታይተዋል” የሚል መረጃ የደረሳቸው ወታደሮች ከደቀምሓረ በሶስት ካሚዮን ተጭነው ወደ ማይዕዳጋ ገሰገሱ። እንደደረሱም መኪናቸውን አቁመው በእግር ወደ ውስጥ ገቡ። አደይ ግደይ “ጦር ሰራዊት መጡብን!” ስትል በህክምና ስራው ላይ ለነበረው ባሏ ነገረችው።

ጀብሃ እዚያች መንደር ገብቶ ማደሩን ኪዳነ ሃኪም ሰምቶ ነበር። እና ወታደሮች ለምን እንደመጡ መገመት አልተቸገረም። ስለዚህ ተጣድፎ ባለቤቱንና ልጆቹን አንድ ክፍል ውስጥ ዘግቶባቸው ሲያበቃ እሱ ወደ ህክምና ክፍሉ ተመለሰ። በዚያው ቅጽበት ጥቂት ወታደሮች ወደ ህክምና ጣቢያው እየተንጋጉ ገቡ።

“ ‘ወንበዴዎችን እያከምክ ነው። መድሃኒትም ሰጥተሃቸዋል’ የሚል መረጃ ደርሶን ነው የመጣነው።” ሲሉ አምባረቁበት።

ኪዳነ ሃኪም ረጋ ብሎ፣ “እኔ የመንግስት ወገን እና የመንግስት ሰራተኛ ነኝ። የሚታከሙትንም መመርመር ትችላላችሁ። ገበሬዎች ናቸው።” ሲል ምላሽ ሰጠ።

የተናገረው አልተዋጠላቸውም።

“ደህና! የምትሰራው ሁሉ ወሬው ደርሶናል።” ሲሉ ዛቱበት።

እንዲህ እየተነጋገሩ ሳለ ከማይሑጻ አግጣጫ የቀላል መሳሪያ ተኩስ ተሰማ። በዚህ ጊዜ ሁለቱ ወታደሮች ተሯሩጠው ከህክምና ጣቢያው ወጥተው ሄዱ።

ከጦርሰራዊት ጋር ተቀላቅሎ መረጃ የሚሰጣቸው እንደነበረ ግልጽ ነበር። ይህም ሰው ማይሑጻ ላይ የገረዝግሄር ተኽለንክኤል እረኛ የነበረ የትግራይ ሰው ነበር። ልጆቻቸው ወደ ትግል የገቡ ሰዎችን ስም፣ ታጋዮች መቼ ወደ መንደሪቷ እንደሚመጡ የመሳሰለውን መረጃ ለማቀበል ነበር በእረኛነት የተቀጠረው። ሁዋላ በግልጽ ጠመንጃ ታጥቆ ከጦር ሰራዊቱ ታይቷል።

ወታደሮቹ አመጣጣችው ህዝቡን አስፈራርተው ለመመለስ ይመስል ነበር። ሆኖም የጀብሃ ተዋጊዎች አሸምቀው በመተኮስ ጥቃት ሲሰነዝሩባቸው በርከት ያሉ ወታደሮች ተገደሉባቸው። ከማለዳ የጀመረ ውጊያ እስከ ቀትር ቀጠለ። የጀብሃ የውጊያ ስልት ውጤታማ ነበር። ጥቂት ተታኩሰው ዘወር እያሉ ብዙ አጠቁ። በሌላ አግጣጫ ደግሞ እንዲሁ አደረጉ፤ ሃይላቸውን እየቆጠቡ ከጥቂት በላይ ወታደሮችን ገድለው ተሰወሩ። ወታደሮቹ የወረደባቸውን ሙትና ቁስለኛ ብዛት ሲገነዘቡ እልሃቸውን የሚወጡበት፤ ቁጣቸውን የሚያበርዱበት ማራገፊያ ፈለጉ። ይህም የመንደሪቷ ነዋሪ ሆነ።

ኪዳነ ሃኪም ወታደሮቹ ከሄዱ በሁዋላ ወደ ቤተሰቡ ተመልሶ ከፋፍሎ አልጋ ስር እንዲደበቁ አደረጋቸው። በዚህ ጊዜ ከደጅ “ክፈትልን” የሚሉ ሰዎች ድምጽ ሰማ። ሲከፍት የዑመር አዜንዳ ሶስት ልጆች ነበሩ። አስገባቸውና ከልጆቹ ጋር አልጋው ስር ጨመራቸው። ከዚያም ክፍሏን ቆልፎ ወደ ስራው ተመለሰ።

ህክምናቸውን የጨረሱ ወንዶችና ሴቶች ከልጆቻቸው ጋር በማስተናገጃው ክፍል ተጠቅጥቀዋል። በተኩሱ ምክንያት መንቀሳቀስ ሰግተው ቁጭ ብለዋል። በፍርሃት ተጨባብጠዋል።

ከተማው ውስጥ ተኩስ እየተሰማ ነበር። የታንክ ተኩስ ድምጽ ጭምር የህክምና ጣቢያውን ግድግዳ አነቃነቀው። ከሰአት 2:00 ሰአት አካባቢ ሰባት የሚሆኑ ወታደሮች በቀጥታ ወደ ሆስፒታሉ መጥተው በደም ፍላት መጮኽ ጀመሩ። ጠመንጃቸውን ኪዳነ ሃኪም ላይ ወደሩ፣

“አንተ ጨምላቃ! አሁኑኑ ወንበዴዎችን ለይተህ ስጠን!”

“እዚህ ወንበዴ የለም። እነዚህ የአካባቢው ገበሬዎች ናቸው።”

አንደኛው ወታደር አይኑን አጕረጠረጠ፣

“ከናንተ መካከል ሰላማዊ የሚባል ሰው የለም። ቀንደኛው ወንበዴ ደግሞ አንተው ራስህ ነህ።” ካለው በሁዋላ በአፈሙዝ እየገፋ ከግድግዳ ጋር አስጠጋው። ሌሎች ወታደሮች ደግሞ ወንድና ሴት ታካሚዎችን ለያዩዋቸው። ወንዶቹን በአንድ ክፍል ውስጥ አስገብተው ወደ ግድግዳው በማስጠጋት ደረደሯቸው። ከዚያም እየፈተሹ በኪሳቸው የነበረውን ገንዘብ፤ በእጃቸው ላይ የታሰረውን ሰአት ወሰዱ።
አንድ ሰው ድምጹን ከፍ አድርጎ ተለማመነ፣

“እባካችሁ ተውን! ሰላማዊ ሰዎች ነን። እኔ የቃኘው የአሜሪካ ካምፕ ሰራተኛ ነኝ። ማስረጃ ወረቀት አለኝ። ተመልከቱ።”

“ዝም በል!” የሚል ምላሽ አገኘ።

አንዱ ወታደር የኪዳነ ሃኪምን ጋዋን አወለቀና ፊቱን ሸፍኖ አሰረው። ከዚያም ሌላውን ወታደር፣ “በሳንጃ ውጋው!” ሲል አዘዘው። ኪዳነ ሃኪም በታካሚዎቹ ፊት ደረቱ ላይ በሳንጃ ተወጋ። ከዚያም በእሩምታ ጥይት ጨረሱት። ኪዳነ ሓኪምን የገደለው ወታደር ወደ ደጅ ከወጣ በሁዋላ ጠመንጃቸውን ወድረው በተጠንቀቅ ለቆሙት ወታደሮች ትእዛዝ ሰጠ። የእሩምታ ተኩስ ድምጽ ታካሚዎቹ ላይ ወረደ። እየተደራረቡ ወደቁ። ከዚያም ወታደሮቹ ሴት ታካሚዎች ወደነበሩበት ክፍል ገቡ። ሆኖም አልገደሉም። አዛዣቸው፣ “ጎበዝ እንሂድ” የሚል ድምጽ ሲያሰማ ተመራርተው ወጡ።

ከተማው ውስጥ ብዙ ሰው ገደሉ። የዑመር ሓጭት ሴት ልጅ ውሃ ተሸክማ ስትሄድ ተኩሰው ገደሏት። የአስር አመት ልጅ ነበረች። አደይ ሄዋን ርቃ ከሄደችበት ስትመለስ መንገድ ላይ አገኟት። ዘንቢል ተሸክማ በመንገድ ተዳክማ ነበር። ሃብቶም ተክኤ እና መብራህቶም እንዲሁ ተገድለው ተገኙ። በእረኛነት ተመስሎ መረጃ ሲለቅም የነበረው ሰው ወታደሮቹን እየመራ ሰው አስፈጀ። እረኛው የጠቆመው ሁሉ ያለ ጥያቄ በቅጽበት ተገደለ።

(የህክምና ጣቢያ ውስጥ በጅምላ ከተተኮሰባቸው መካከል ኪዳነ ገረየሱስ የተባለ ሰው ሬሳ ተጭኖት ከሞት ተረፈ። ክፉኛ በመቁሰሉ ግን አንድ እጁ ተቆረጠ። ታሪኩን ለመተክም በቃ። የኪዳነ ሃኪም ልጆች ከሞት አመለጡ። ስምንቱም ልጆቹ፣ ከእናታቸው ጋር ወደ በረሃ በመሄድም ትግሉን ተቀላቀሉ። ልጆቹ በተዋጊ ሰራዊት፣ በከባድ መሳሪያ፣ በህክምና፣ በወታደራዊ ስለላ ክፍሎች ተመድበው ታገሉ። የኪዳነ የመጨረሻ ልጅ ሰናይት የሄሊኮፕተር አብራሪ የሆነች ሲሆን፤ በወያኔ ወረራ ጊዜም በጦርነቱ ተካፍላለች።)

ተራኪዎች ኪዳነ ገሬሱስ፣ ትርሓስ ኪዳነ፣ ሓሊማ ኣድም፡ ዳኒ ዑመር
ማጣቀሻ ፡ ሕድሪ መጽሔት 2008 ቁጥር 37
ጸሓፊ፡ ገነት ስዩም
ኣርታኢና ተርጓሚ፡ ተስፋዬ ገብረኣብ

Wedi
Member+
Posts: 7994
Joined: 29 Jan 2020, 21:44

Re: ኪዳነ ሓኪምና ታካሚዎቹ - ካልተነገሩት መራር ታሪኮች በጭልፋ

Post by Wedi » 23 Dec 2020, 07:43

ተስፋዬ ገብረኣብ is not trust worthy author. If you trust ተስፋዬ ገብረኣብ, then you are going to trust his books on TPLF entitled "ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ".and his another book entitled "የቡርቃ ዝምታ". All his writings and books are fictions which doesn't exist on the ground. As you have seen it with your own eyes, TPLF is not "ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ" rather it is a bunch of gangs who evaporated in 15 days war like morning dew.

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ኪዳነ ሓኪምና ታካሚዎቹ - ካልተነገሩት መራር ታሪኮች በጭልፋ

Post by Meleket » 23 Dec 2020, 09:45

ወዳጃችን Wedi ጥቆማህ መልካም ነበር፣ ቢሆንም ግን ቅሉ ይህ ታሪክ በእርግጥ እንደተፈጸመ በአካል ስለምናውቅና ተራኪዎቹንም ሆኑ ጸሓፊዋን ስለምናውቅ፣ እኛ ያመንበትን ግን ደግሞ ያልተነገረውን የኤርትራ ህዝብ ታሪክና ትረካ ነው ለኢትዮጵያዉያን ወንድሞቻችን የምናቀርበው። በዚህ ታሪክ ውስጥ የጋዜጠኛና የደራሲው የተስፋዬ ገብረኣብ ስራ አርትኦትና ወደ ያፍሪካቀንድ ቋንቋ ማለትም ወደ አማርኛ መተርጎም ብቻ ነው። :mrgreen: እኛ በትግርኛ የተጻፈውንም ስለምናውቀው ስጋት አይግባህ ግሩም አድርጎ ነው ተስፋዬ የተረጎመው።

ከዚያ በተረፈ ጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋዬ ገብረኣብ፣ “ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ” ምናምን እያለ ወያኔን እያሞካሸ ሲጽፍላቸውም፡ “ወያኔዎቹ ርእሲ ዓዲ የተባለውን ኤርትራዊ ተራራ መውጣት አቅቷቸው፡ እነ ስዬ ኣብርሃም ጭምር በሻዕቢያ ጫንቃ ታዝለው ርእሲ ዓዲ የተባለውን ተራራ ለስልጠና እንደወጡም ቁልጭ አድርጎ በምትሃታዊው ቅኔው ገልጾልናል”። በመሆኑም ወንድማችን ተስፋዬ ገብረኣብ ደህና አድርጎ የቤትስራውን የሰራ ቢሾፍቱ ላይ የበቀለ ለኤርትራ ህዝብ ትግል መጎልበት እንዲሁም ለኦሮሞ ህዝብ ትግልም ጭምር የራሱን የማይናቅ ሚና ያበረከተ ብርቅ ጸሓፊ ነው። የአማርኛና የኦሮሚፋ የመጻፍ ችሎታውን የማያደንቅ ፍጥረት የለም። ወደድንም ጠላንም የሶስተኛው ዓለም ጋዜጠኛ መሆኑንም መዘንጋት የለብንም። :mrgreen: ማንን ለማስደሰት ምን ብሎ እንደሚጽፍ መዘንጋት የለብንም፡ አንዳንዴም ዓይናቸውን ያፈጠጡ ሃቆችን ለመግለጥ ድፍረት ሊጎድለው ይችላል፡ አንዳንዴም መጠቀስ የሚገባቸውን ላይጠቅስ ይችላል፡ ወዘተ ወዘተ ይህ ደግሞ የአብዛኞቹ የሶስተኛው ዓለም ጋዜጠኞች መለያ ባህርይ መሆኑን አንስተውም። ተስፋዬ የማያዋጣ ከመሰለው አንዳንድ ታሪኮችንም ሸፈፍ ብሎ ሊያልፋቸው ይችላል፡ አንዳንዴም በደንብ ስለማያውቀው ነገርም ሲጽፍ “አዋቂዎች” ኣግኝተው ሲገስጹት ሰምተናል፡ ተስፋዬ ሲፈልግ ደግሞ አንዳንዱን ታሪክ በደንብ አድርጎ ከስር ከመሰረቱ ጎልጉሎ ሲያወጣም ተስተውሏል። በዚህ እንደተካነ ኤርትራዉያን ሆንን ኢትዮጵያዉያን አንባቢዎቹ አንስተውም።

ያም ሆነ ይህ ግን፡ ይህ ትረካም የሚገኝበትን፡ የተለያዩ ኤርትራዉያን ጸሓፊዎች በትግርኛ የጻፉትን ስራ በደንብ አድርጎ ተርጕሞ “ያልተነገሩ ታሪኮች” በሚል ርእስ ያሰፈረውን ትረካ አልፎ አልፎ በጭልፋ እየጨለፍን ለኢትዮጵያዉያን ወንድሞቻችን እንካችሁ ተቋደሱ የኤርትራ ህዝብን ታሪክ ማለታችንን እንቀጥላለን።
:mrgreen:

Wedi wrote:
23 Dec 2020, 07:43
ተስፋዬ ገብረኣብ is not trust worthy author. If you trust ተስፋዬ ገብረኣብ, then you are going to trust his books on TPLF entitled "ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ".and his another book entitled "የቡርቃ ዝምታ". All his writings and books are fictions which doesn't exist on the ground. As you have seen it with your own eyes, TPLF is not "ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ" rather it is a bunch of gangs who evaporated in 15 days war like morning dew.

Meleket
Member
Posts: 3057
Joined: 16 Feb 2018, 05:08

Re: ኪዳነ ሓኪምና ታካሚዎቹ - ካልተነገሩት መራር ታሪኮች በጭልፋ

Post by Meleket » 23 Dec 2020, 09:56

ሓውና Sabur መስተንክራዊ ጽንዓት ዝዓሰሎ ታሪክ ህዝብና ደኣ ንሕና ዘይገለጽናዮ መን ኪገልጾ፣ ታሪኽና ግዳይ ጨወይቲ-ታሪኽ ኪከውን ኣይከነፍቕድን ኢና።

ብርግጽ ንነፍስ ወከፍ ዓዲ ኣብ ሃገርና ነናታ ዘይተነግረ ታሪኽ ከዚና ከምዘላ ፍሉጥ ኢዩ፣ ዕዮና ነቱይ ታሪኽ ህዝብና ፈታውን ጸላኢን ከምዝፈልጦ ምግባር እዩ።

ኃይለሥላሴ ኣምሃራይ ኪከውን ይኽእል ይከውን (ርግጸይና ኣይኾንኩን :lol: )፡ ካብ ደርጊ መንግሥቱ ኃይለማርያምን ምኽትሉ ፍስሓ ደስታን፡ ካብ ኢህኣዲግ መለስ ዜናዊ ኮነ ኃይለማርያም ደሳለኝ ኣምሃሩ ኣይኾኑን። ጊደ ሓቂ እዙይ ገሊጭናዮ ዛሎና ታሪኽ ሕዝብና፡ ዓሌቶም ብዘየገድስ ብገዛእቲ ደርብታት ናይ ኢጦብያ ዝተፈጸመ ግፍዒ ኢዩ። ክንርስዖ ድማ ኣይግባእን።
:mrgreen:
Sabur wrote:
23 Dec 2020, 07:30

Thank you Meleket !!

Every Village, Every Town, and Every City in Eritrea carries deep scars of The Brutal Atrocities of Innocent Eritreans by the Amhara Led Ethiopian Colonizer Forces.

Eritrea Shall Not forget.

Viva Eritrea !!!

Eritrea for Eritreans !!!


Meleket wrote:
23 Dec 2020, 05:02
ጃንሆይና ደርግ ካልተነገሩት መራር ታሪኮች (ገጽ 171-174)

“ማይሑጻ በተባለው አካባቢ ወንበዴዎች ታይተዋል” የሚል መረጃ የደረሳቸው ወታደሮች ከደቀምሓረ በሶስት ካሚዮን ተጭነው ወደ ማይዕዳጋ ገሰገሱ። እንደደረሱም መኪናቸውን አቁመው በእግር ወደ ውስጥ ገቡ። አደይ ግደይ “ጦር ሰራዊት መጡብን!” ስትል በህክምና ስራው ላይ ለነበረው ባሏ ነገረችው።

ጀብሃ እዚያች መንደር ገብቶ ማደሩን ኪዳነ ሃኪም ሰምቶ ነበር። እና ወታደሮች ለምን እንደመጡ መገመት አልተቸገረም። ስለዚህ ተጣድፎ ባለቤቱንና ልጆቹን አንድ ክፍል ውስጥ ዘግቶባቸው ሲያበቃ እሱ ወደ ህክምና ክፍሉ ተመለሰ። በዚያው ቅጽበት ጥቂት ወታደሮች ወደ ህክምና ጣቢያው እየተንጋጉ ገቡ።

“ ‘ወንበዴዎችን እያከምክ ነው። መድሃኒትም ሰጥተሃቸዋል’ የሚል መረጃ ደርሶን ነው የመጣነው።” ሲሉ አምባረቁበት።

ኪዳነ ሃኪም ረጋ ብሎ፣ “እኔ የመንግስት ወገን እና የመንግስት ሰራተኛ ነኝ። የሚታከሙትንም መመርመር ትችላላችሁ። ገበሬዎች ናቸው።” ሲል ምላሽ ሰጠ።

የተናገረው አልተዋጠላቸውም።

“ደህና! የምትሰራው ሁሉ ወሬው ደርሶናል።” ሲሉ ዛቱበት።

እንዲህ እየተነጋገሩ ሳለ ከማይሑጻ አግጣጫ የቀላል መሳሪያ ተኩስ ተሰማ። በዚህ ጊዜ ሁለቱ ወታደሮች ተሯሩጠው ከህክምና ጣቢያው ወጥተው ሄዱ።

ከጦርሰራዊት ጋር ተቀላቅሎ መረጃ የሚሰጣቸው እንደነበረ ግልጽ ነበር። ይህም ሰው ማይሑጻ ላይ የገረዝግሄር ተኽለንክኤል እረኛ የነበረ የትግራይ ሰው ነበር። ልጆቻቸው ወደ ትግል የገቡ ሰዎችን ስም፣ ታጋዮች መቼ ወደ መንደሪቷ እንደሚመጡ የመሳሰለውን መረጃ ለማቀበል ነበር በእረኛነት የተቀጠረው። ሁዋላ በግልጽ ጠመንጃ ታጥቆ ከጦር ሰራዊቱ ታይቷል።

ወታደሮቹ አመጣጣችው ህዝቡን አስፈራርተው ለመመለስ ይመስል ነበር። ሆኖም የጀብሃ ተዋጊዎች አሸምቀው በመተኮስ ጥቃት ሲሰነዝሩባቸው በርከት ያሉ ወታደሮች ተገደሉባቸው። ከማለዳ የጀመረ ውጊያ እስከ ቀትር ቀጠለ። የጀብሃ የውጊያ ስልት ውጤታማ ነበር። ጥቂት ተታኩሰው ዘወር እያሉ ብዙ አጠቁ። በሌላ አግጣጫ ደግሞ እንዲሁ አደረጉ፤ ሃይላቸውን እየቆጠቡ ከጥቂት በላይ ወታደሮችን ገድለው ተሰወሩ። ወታደሮቹ የወረደባቸውን ሙትና ቁስለኛ ብዛት ሲገነዘቡ እልሃቸውን የሚወጡበት፤ ቁጣቸውን የሚያበርዱበት ማራገፊያ ፈለጉ። ይህም የመንደሪቷ ነዋሪ ሆነ።

ኪዳነ ሃኪም ወታደሮቹ ከሄዱ በሁዋላ ወደ ቤተሰቡ ተመልሶ ከፋፍሎ አልጋ ስር እንዲደበቁ አደረጋቸው። በዚህ ጊዜ ከደጅ “ክፈትልን” የሚሉ ሰዎች ድምጽ ሰማ። ሲከፍት የዑመር አዜንዳ ሶስት ልጆች ነበሩ። አስገባቸውና ከልጆቹ ጋር አልጋው ስር ጨመራቸው። ከዚያም ክፍሏን ቆልፎ ወደ ስራው ተመለሰ።

ህክምናቸውን የጨረሱ ወንዶችና ሴቶች ከልጆቻቸው ጋር በማስተናገጃው ክፍል ተጠቅጥቀዋል። በተኩሱ ምክንያት መንቀሳቀስ ሰግተው ቁጭ ብለዋል። በፍርሃት ተጨባብጠዋል።

ከተማው ውስጥ ተኩስ እየተሰማ ነበር። የታንክ ተኩስ ድምጽ ጭምር የህክምና ጣቢያውን ግድግዳ አነቃነቀው። ከሰአት 2:00 ሰአት አካባቢ ሰባት የሚሆኑ ወታደሮች በቀጥታ ወደ ሆስፒታሉ መጥተው በደም ፍላት መጮኽ ጀመሩ። ጠመንጃቸውን ኪዳነ ሃኪም ላይ ወደሩ፣

“አንተ ጨምላቃ! አሁኑኑ ወንበዴዎችን ለይተህ ስጠን!”

“እዚህ ወንበዴ የለም። እነዚህ የአካባቢው ገበሬዎች ናቸው።”

አንደኛው ወታደር አይኑን አጕረጠረጠ፣

“ከናንተ መካከል ሰላማዊ የሚባል ሰው የለም። ቀንደኛው ወንበዴ ደግሞ አንተው ራስህ ነህ።” ካለው በሁዋላ በአፈሙዝ እየገፋ ከግድግዳ ጋር አስጠጋው። ሌሎች ወታደሮች ደግሞ ወንድና ሴት ታካሚዎችን ለያዩዋቸው። ወንዶቹን በአንድ ክፍል ውስጥ አስገብተው ወደ ግድግዳው በማስጠጋት ደረደሯቸው። ከዚያም እየፈተሹ በኪሳቸው የነበረውን ገንዘብ፤ በእጃቸው ላይ የታሰረውን ሰአት ወሰዱ።
አንድ ሰው ድምጹን ከፍ አድርጎ ተለማመነ፣

“እባካችሁ ተውን! ሰላማዊ ሰዎች ነን። እኔ የቃኘው የአሜሪካ ካምፕ ሰራተኛ ነኝ። ማስረጃ ወረቀት አለኝ። ተመልከቱ።”

“ዝም በል!” የሚል ምላሽ አገኘ።

አንዱ ወታደር የኪዳነ ሃኪምን ጋዋን አወለቀና ፊቱን ሸፍኖ አሰረው። ከዚያም ሌላውን ወታደር፣ “በሳንጃ ውጋው!” ሲል አዘዘው። ኪዳነ ሃኪም በታካሚዎቹ ፊት ደረቱ ላይ በሳንጃ ተወጋ። ከዚያም በእሩምታ ጥይት ጨረሱት። ኪዳነ ሓኪምን የገደለው ወታደር ወደ ደጅ ከወጣ በሁዋላ ጠመንጃቸውን ወድረው በተጠንቀቅ ለቆሙት ወታደሮች ትእዛዝ ሰጠ። የእሩምታ ተኩስ ድምጽ ታካሚዎቹ ላይ ወረደ። እየተደራረቡ ወደቁ። ከዚያም ወታደሮቹ ሴት ታካሚዎች ወደነበሩበት ክፍል ገቡ። ሆኖም አልገደሉም። አዛዣቸው፣ “ጎበዝ እንሂድ” የሚል ድምጽ ሲያሰማ ተመራርተው ወጡ።

ከተማው ውስጥ ብዙ ሰው ገደሉ። የዑመር ሓጭት ሴት ልጅ ውሃ ተሸክማ ስትሄድ ተኩሰው ገደሏት። የአስር አመት ልጅ ነበረች። አደይ ሄዋን ርቃ ከሄደችበት ስትመለስ መንገድ ላይ አገኟት። ዘንቢል ተሸክማ በመንገድ ተዳክማ ነበር። ሃብቶም ተክኤ እና መብራህቶም እንዲሁ ተገድለው ተገኙ። በእረኛነት ተመስሎ መረጃ ሲለቅም የነበረው ሰው ወታደሮቹን እየመራ ሰው አስፈጀ። እረኛው የጠቆመው ሁሉ ያለ ጥያቄ በቅጽበት ተገደለ።

(የህክምና ጣቢያ ውስጥ በጅምላ ከተተኮሰባቸው መካከል ኪዳነ ገረየሱስ የተባለ ሰው ሬሳ ተጭኖት ከሞት ተረፈ። ክፉኛ በመቁሰሉ ግን አንድ እጁ ተቆረጠ። ታሪኩን ለመተክም በቃ። የኪዳነ ሃኪም ልጆች ከሞት አመለጡ። ስምንቱም ልጆቹ፣ ከእናታቸው ጋር ወደ በረሃ በመሄድም ትግሉን ተቀላቀሉ። ልጆቹ በተዋጊ ሰራዊት፣ በከባድ መሳሪያ፣ በህክምና፣ በወታደራዊ ስለላ ክፍሎች ተመድበው ታገሉ። የኪዳነ የመጨረሻ ልጅ ሰናይት የሄሊኮፕተር አብራሪ የሆነች ሲሆን፤ በወያኔ ወረራ ጊዜም በጦርነቱ ተካፍላለች።)

ተራኪዎች ኪዳነ ገሬሱስ፣ ትርሓስ ኪዳነ፣ ሓሊማ ኣድም፡ ዳኒ ዑመር
ማጣቀሻ ፡ ሕድሪ መጽሔት 2008 ቁጥር 37
ጸሓፊ፡ ገነት ስዩም
ኣርታኢና ተርጓሚ፡ ተስፋዬ ገብረኣብ

ZEMEN
Member
Posts: 2493
Joined: 27 Jun 2011, 14:37

Re: ኪዳነ ሓኪምና ታካሚዎቹ - ካልተነገሩት መራር ታሪኮች በጭልፋ

Post by ZEMEN » 23 Dec 2020, 10:10

Wedi wrote:
23 Dec 2020, 07:43
ተስፋዬ ገብረኣብ is not trust worthy author. If you trust ተስፋዬ ገብረኣብ, then you are going to trust his books on TPLF entitled "ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ".and his another book entitled "የቡርቃ ዝምታ". All his writings and books are fictions which doesn't exist on the ground. As you have seen it with your own eyes, TPLF is not "ተራሮችን ያንቀጠቀጠ ትውልድ" rather it is a bunch of gangs who evaporated in 15 days war like morning dew.
He didn't write the sad story. He simply is a translator. from what understood.

Aurorae Borealis
Member
Posts: 303
Joined: 14 Nov 2020, 23:41

Re: ኪዳነ ሓኪምና ታካሚዎቹ - ካልተነገሩት መራር ታሪኮች በጭልፋ

Post by Aurorae Borealis » 23 Dec 2020, 10:44

Wedi,

Tragic stories such as above were typical in the 1960's to 1980's of Eritrea. Many Tigrayans recruited by the Ethiopian governments poisoned water sources and wells in Eritrean villages. young Senait, the helicopter pilot, serving her country and people brings tears to my eyes. That is tears of joy.

Post Reply