-
- Member
- Posts: 4663
- Joined: 21 Apr 2015, 12:18
አቢቹ 3 ቀን deadline ቆጠራ weekend አይጨምርም አለ።
In the mean time the ልሙጣውያን still holding their breath
-
- Member+
- Posts: 7694
- Joined: 15 Oct 2016, 10:31
-
- Member
- Posts: 4077
- Joined: 15 Jun 2018, 17:40
Re: አቢቹ 3 ቀን deadline ቆጠራ weekend አይጨምርም አለ።
Happy now?
ሕዳር 17 ቀን 2013
የጦር ሀይሎች ጠ/አዛዥና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የመከላከያ ሰራዊታችን የመጨረሻውንና ሶስተኛውን የዘመቻ ምዕራፍ እንዲፈፅም ትዕዛዝ ሰጡ ፡፡
የመከላከያ ሰራዊታችን በሰላማዊ ዜጎች ፣ በቅርሶች ፣ በቤተ እምነቶች ፣ በልማት ተቋማትና በንብረቶች ላይ ጉዳት ሳይደርስ ጁንታውን ለህግ የሚያቀርብበትን ጥንቃቄ የተሞላው የዘመቻ ስልት መንደፉን አረጋግጠዋል ባወጡት መግለጫ።
የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦
የመጨረሻው የዘመቻው ምእራፍ ተጀምሯል።
የተሰጠው የ72 ሰዓት ጊዜ ተጠናቋል፤ ህግ የማስከበር ዘመቻው የመጨረሸው ምእራፍ ላይ ደርሷል። በተሰጠው የ72 ሰዓት ጊዜ ውስጥ በሺህዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ልዩ ሀይል እና ሚሊሻ አባላት እጃቸውን ለመከላከያ ሰራዊት ሰጥተዋል።
ብዙ የትግራይ ወጣቶችም የህወሓትን እኩይ አላማ ተረድተው እጃቸውን ሰብስበዋል። ይህ በመጨረሻው ሰዓትም ቢሆን የተወሰደ ሀላፊነት የሚሰወማው ውሳኔ ህሊና ካለው ፍጡር የሚጠበቅ ውሳኔ ነው።
መንግስት 72 ሰዓት ሲሰጥ አላማው ሁለት ነበር። በአንድ በኩል ዋና ፍላጎቱ ህግ ማስከበር እንጅ ጦርነት አለመሆኑን መግለጥ ነው።
አንደኛው ፣ ጁንታው በሰላም እጁን ለመስጠት ከቻለ ዘመቻውን በማጠናቀቅ ህግን በአነስተኛ ዋጋ ለማስከበር ይቻላል ብሎ ያምናል። ለዚህም ሲባል ተደጋጋሚ እድሎችን ሰጥቶ ነበር።
ሁለተኛው ደግሞ ፣ የህወሓት የጥፋት አላማ ዘግይቶም ቢሆን የገባው አንድም ሰው ከተገኘ ያንን ሰው ለማትረፍ እንዲቻል ነው።
ለህወሓት ጁንታ የተከፈተው የመጨረሻ ሰላማዊ በር በጁንታው እብሪት ምክንያት ተዘግቷል። የጥፋታቸውን አላማ ተገንዝቦ ለሚመለስ ሰው በተከፈተው በር ግን፤ በሺህዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ሚሊሻ እና ልዩ ሀይል አባላት እጃቸውን እየሰጡ ገብተውበታል።
የመከላከያ ሰራዊታችን የመጨረሻውን እና ሶስተኛውን የዘመቻ ምዕራፍ እንዲፈፅም ትዕዛዝ ተሰጥቶታል። በዚህ ዘመቻ ለንፁሃን ሰዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እናደርጋለን፤ በህዝባችን ላብ የተሰራችው የመቐለ ከተማ የከፋ ጉዳት እንዳያገኛት የሚቻለውን ሁሉ ያደርጋል።
ቅርሶች ፣ ቤተ እምነቶች ፣ የህዝብ መገልገያዎች ፣ የልማት ተቋማት እና የህዝብ መኖሪያዎች የጥቃት ኢላማ እንዳይሆኑ ሁሉም አይነት ጥንቃቄ ይደረጋል።
የመቐለና የአካባቢው ህዝባችን ትጥቁን ፈትቶ በቤቱ በመቀመጥና ከወታደራዊ ዒላማዎች በመራቅ፤ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሁሉ እንዲያደርግ ጥሪ እናቀርባለን።
በጥቂት የህወሓት ጁንታ አባላት ምክንያት የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ህዝቡ የጁንታውን አባላት አሳልፎ በመስጠት የበኩሉን አስተዋጽዖ እንዲያደርግ ጥሪ እናደርጋለን።
የመከላከያ ሰራዊታችን በሰላማዊ ዜጎች፣ በቅርሶች፣ በቤተ እምነቶች፣ በልማት ተቋማትና በንብረቶች ላይ ጉዳት ሳይደርስ ጁንታውን ለህግ የሚያቀርብበትን ጥንቃቄ የተሞላው የዘመቻ ስልት የነደፈ መሆኑን ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።
ሕዳር 17 ቀን 2013
የጦር ሀይሎች ጠ/አዛዥና ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የመከላከያ ሰራዊታችን የመጨረሻውንና ሶስተኛውን የዘመቻ ምዕራፍ እንዲፈፅም ትዕዛዝ ሰጡ ፡፡
የመከላከያ ሰራዊታችን በሰላማዊ ዜጎች ፣ በቅርሶች ፣ በቤተ እምነቶች ፣ በልማት ተቋማትና በንብረቶች ላይ ጉዳት ሳይደርስ ጁንታውን ለህግ የሚያቀርብበትን ጥንቃቄ የተሞላው የዘመቻ ስልት መንደፉን አረጋግጠዋል ባወጡት መግለጫ።
የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦
የመጨረሻው የዘመቻው ምእራፍ ተጀምሯል።
የተሰጠው የ72 ሰዓት ጊዜ ተጠናቋል፤ ህግ የማስከበር ዘመቻው የመጨረሸው ምእራፍ ላይ ደርሷል። በተሰጠው የ72 ሰዓት ጊዜ ውስጥ በሺህዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ልዩ ሀይል እና ሚሊሻ አባላት እጃቸውን ለመከላከያ ሰራዊት ሰጥተዋል።
ብዙ የትግራይ ወጣቶችም የህወሓትን እኩይ አላማ ተረድተው እጃቸውን ሰብስበዋል። ይህ በመጨረሻው ሰዓትም ቢሆን የተወሰደ ሀላፊነት የሚሰወማው ውሳኔ ህሊና ካለው ፍጡር የሚጠበቅ ውሳኔ ነው።
መንግስት 72 ሰዓት ሲሰጥ አላማው ሁለት ነበር። በአንድ በኩል ዋና ፍላጎቱ ህግ ማስከበር እንጅ ጦርነት አለመሆኑን መግለጥ ነው።
አንደኛው ፣ ጁንታው በሰላም እጁን ለመስጠት ከቻለ ዘመቻውን በማጠናቀቅ ህግን በአነስተኛ ዋጋ ለማስከበር ይቻላል ብሎ ያምናል። ለዚህም ሲባል ተደጋጋሚ እድሎችን ሰጥቶ ነበር።
ሁለተኛው ደግሞ ፣ የህወሓት የጥፋት አላማ ዘግይቶም ቢሆን የገባው አንድም ሰው ከተገኘ ያንን ሰው ለማትረፍ እንዲቻል ነው።
ለህወሓት ጁንታ የተከፈተው የመጨረሻ ሰላማዊ በር በጁንታው እብሪት ምክንያት ተዘግቷል። የጥፋታቸውን አላማ ተገንዝቦ ለሚመለስ ሰው በተከፈተው በር ግን፤ በሺህዎች የሚቆጠሩ የትግራይ ሚሊሻ እና ልዩ ሀይል አባላት እጃቸውን እየሰጡ ገብተውበታል።
የመከላከያ ሰራዊታችን የመጨረሻውን እና ሶስተኛውን የዘመቻ ምዕራፍ እንዲፈፅም ትዕዛዝ ተሰጥቶታል። በዚህ ዘመቻ ለንፁሃን ሰዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እናደርጋለን፤ በህዝባችን ላብ የተሰራችው የመቐለ ከተማ የከፋ ጉዳት እንዳያገኛት የሚቻለውን ሁሉ ያደርጋል።
ቅርሶች ፣ ቤተ እምነቶች ፣ የህዝብ መገልገያዎች ፣ የልማት ተቋማት እና የህዝብ መኖሪያዎች የጥቃት ኢላማ እንዳይሆኑ ሁሉም አይነት ጥንቃቄ ይደረጋል።
የመቐለና የአካባቢው ህዝባችን ትጥቁን ፈትቶ በቤቱ በመቀመጥና ከወታደራዊ ዒላማዎች በመራቅ፤ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ሁሉ እንዲያደርግ ጥሪ እናቀርባለን።
በጥቂት የህወሓት ጁንታ አባላት ምክንያት የሚደርሰውን ጉዳት ለመቀነስ ህዝቡ የጁንታውን አባላት አሳልፎ በመስጠት የበኩሉን አስተዋጽዖ እንዲያደርግ ጥሪ እናደርጋለን።
የመከላከያ ሰራዊታችን በሰላማዊ ዜጎች፣ በቅርሶች፣ በቤተ እምነቶች፣ በልማት ተቋማትና በንብረቶች ላይ ጉዳት ሳይደርስ ጁንታውን ለህግ የሚያቀርብበትን ጥንቃቄ የተሞላው የዘመቻ ስልት የነደፈ መሆኑን ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን።
-
- Member
- Posts: 4663
- Joined: 21 Apr 2015, 12:18
Re: አቢቹ 3 ቀን deadline ቆጠራ weekend አይጨምርም አለ።
This becoming like a child’s play. Counting...Tizaz settu..counting..15 km kerrachew..counting..Tizaz settu..