Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 30903
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

የቤተ ጉራጌ ባህላዊ ሸንጎ

Post by Horus » 31 Oct 2020, 00:17

በመላ ኢትዮጵያ የዘር ሽብር፣ ቀውስ፣ አናርኪ፣ ጥላቻ፣ ክፍፍል፣ ውድቀት፣ ዝቅጠት፣ ውዥንብር፣ እውቀት፣ ጥበብ፣ ብልህነት ፣ ኢንተለጀንስ በጠፋበት በዚህ ዘመን ጉራጌ ራሱን እንደ አለት በጸና ባባቶቹ ካልችርና እሴት ስረ መሰረት አንድንቱን እንደ ብረት እያገንታ፣ እያበረታ ነው !!! ኤቦ ለጉራጌ ባሊቆች፣ ለጉራጌ ሊቆች፣ ለጉራጌ ጉርዛዘ !!!


Horus
Senior Member+
Posts: 30903
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: የቤተ ጉራጌ ባህላዊ ሸንጎ

Post by Horus » 31 Oct 2020, 01:02

አያችሁ በዊዝደም፣ በጥበብ መመራት ማለት ይህ ነው ። እስቲ ልብ ብላችሁ ተመልከቱ ። ትግሬ ተክፋፍሏል ። አማራ ተከፋፍሏል፣ ኦሮሞ ተከፋፍሏል ፣ የጎሳ ክልል፣ ጎስኘት ራሱ ጎሳውን ነው የሚከፋፍል ። የጉራጌ ወጣቶች ክልል እንፈልጋለን ብለው ሲነሱ እንደ ሌሎቹ ክልሎች ያገሩ አዋቂ፣ ባሊቅ፣ ዋይዝ ፣ ጉሩዞች በወጣቱ አልተነዱም ። ወጣቱን ሰብስብው የዚህ ንቅናቄ ሁሉ ቁልፍ አላማ ምን እንደ ሆነ አስተማሯቸው፤ እሱም የጉራጌ አንድነት እና የጉራጌ ስላም መሆኑን!!! ይህ ነው የሰከነ ሕዝብ፣ የሰክነ ካልቸር ማለት ። በጉራጌ ሁሉ ያሉትን ታሪካዊ፣ ባህላዊ፣ ክቡር ስርዓቶችን ስብስበው በአንድ ጉባኤ አቆሙና (ቤተ ጉራጌ ባህላዊ ሸንጎ) መሪነት ለወጣቱ አዘዙ ። አሁን ሂዱና ለጉራጌ ራስ ገዥነት ታገሉ አሉ ። ልጅ የሚመራው ባባቱ ነው እንጂ የተገላቢጦሽ አይደለም፤ ያውም ከሊስትሮ ተነስተው ፎቅ የሰሩ ሽማግሎች ባሉበት ቤተ ጉራጌ !!!

Post Reply