Please wait, video is loading...
የፌዴራል መንግስት በህወሓትን ላይ እርምጃ አለመውሰዱን ተከትሎ ህወሓት በትግራይ ውስጥ የሚገኙ ተቃዋሚዎችን እየፈነና እየረሸነ ነው። በተለይም ወጣቱን ክፍል የለውጥ አቀንቃኝ በሚል ፍረጃ በሌሊት እያፈነ ወደ አልታወቀ ቦታ እንደሚወስድ የታወቀ ሲሆን፣ በበርካታ ወጣቶች ላይ የአካል ማጉደልና ግዲያ እየተፈፀመባቸው ይገኛል።
ህወሓት ከ1983 ዓ/ም ጀምሮ በተለያዩ የትግራይ በረሃማ ቦታዎች በርካታ ጥልቀት እና ስፋት ያላቸውን እንደ ባዶ 6 እና 8 የመሳሰሉ የማሰቃያ ጉዲጓዶችን ለ10 አመት ያህል ያለማቋረጥ በትግራይ ገበሬ በማስቆፈር የጎንዴር አማራን በተለይም የወልቃይት፣ የጠገዴና የቃፍታ ሁመራን አማራዎች በጅምላ ያስርበትና በጪስ አፍኖ ይገድልበት ነበር። ሆኖም ከ1997 ዓ/ም ወዲህ በመላ ሀገሪቱ በህወሓት ላይ ተቃውሞ በመቀስቀሱ እና የእስረኛው ቁጥር በመጨመሩ ህወሓት እስረኞች በትግራይ በረሃማ ቦታዎች ጥልቀት ያላቸው ጉዲጓድ እንድቆፈሩ አዘዘ።
ህወሓት ስለሚቆፈሩት ጥልቅ ጉዲጓዶች ለትግራይ ህዝብ በካዲሪዎቹ አማካኝነት ከቀበሌ እስከ ዞን የሚያስተላልፈው መልዕክት እንዲህ ነበር። "ወልቃይት እና ራያ የትግራይ ህዝብ የዴም ካሳ ናቸው። ወልቃይት እና ራያን ከአማራው ላይ ነጥቀን ያመጣነው ከ70,000 ሺህ በላይ የትግራይ ወጣቶችን ሰውተን ነው። እነዚህን ግዛቶች የአማራ ናቸው፣ ወልቃይት እና ራያ የአማራ ነው የሚል አማራ ይገባባቸዋል፣ የሚቆፈሩት ጉዲጓዶች ዋና አላማ ይሔው ነው። ጉዲጓዶቹ የትግራይን ጥላቶች የሚያወድሙ እንጅ የትግራይን ህዝብ የሚጎዱ አይደለም።" የሚል ነበር።
ዛሬ ግን በእነዚያ ጥልቅ ጉድጓዶች ህወሓት የትግራይን ወጣት በሌሊት እያፈነ እየጨመረ ይገኛል። ከጥቅምት ወር 2012 ዓ/ም ጀምሮ እስከ አሁኑ ቀን ድረስ ከ10,000 ሺህ በላይ የትግራይ ወጣቶች ታፍነዋል። ከ2500 በላይ ትግራዊ በህወሓት አፋኝ ኃይል ተገድለዋል። ይሔን ሁሉ ግፍ ህወሓት በትግራይ ህዝብና ወጣት ላይ የሚፈፅመው ሀገሪቱን የሚመራት መንግስት ቸልተኛ መሆኑ ነው።
የፌዴራል መንግስት በተለይም የትግራይን ህዝብ የረሳውና ከኢትዮጵያዊነት ያወጣው እስከ መምሰል ደርሷል። ያ ባይሆን ኑሮ ህወሓት በትግራይ ህዝብ ላይ ከፍተኛ የሆነ የሰብአዊ ጥሰት እና የጅምላ ግዲያ ሲፈፅም በዝምታና በቸልተኝነት መንግስት አይመለከተውም ነበር።
የእውነት መንግስት ካለ የእውነት የትግራይን ህዝብ እንደ ሌሎቹ ህዝቦች መንግስት በእኩል አይን የሚመለከት ከሆነ ዛሬ ነገ ሳይል በአፋጣኝ በህወሓት ላይ እርምጃ ይውሰድልን። በኃይል የተጫነንን ህወሓትን ያስወግድልን። መንግስት ህወሓትን ለማስወገድ ለሚወስዴው እርምጃ መላው ተጋሩ ከመንግስት ጎን ነን።
ህወሓት ከኢትዮጵያ ምድር መወገድ ያለበት ቡድን ነው።