Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Revelations
Senior Member+
Posts: 33672
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

የሕዳሴው ግድብ ቀጣይ የድርድር አጀንዳዎች [ዋዜማ ሬዲዮ]

Post by Revelations » 28 Jun 2020, 14:50

Please wait, video is loading...

Revelations
Senior Member+
Posts: 33672
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: የሕዳሴው ግድብ ቀጣይ የድርድር አጀንዳዎች [ዋዜማ ሬዲዮ]

Post by Revelations » 28 Jun 2020, 15:10

በአፍሪቃ ህብረት አደራዳሪነት በተደረገው ውይይት ላይ ሀገራቱ በሕዳሴው ግድብ ዙሪያ ድርድራቸውን ለመቀጠል የተሰማሙ ሲሆን ከማናቸውም አደናቃፊ መግለጫዎች ለመታቀብ ተስማምተው ነበር።

ይሁንና የግብፅና የሱዳን መንግስታት ኢትዮጵያ ግድቡን ለመሙላት የያዘችውን እቅድ ለማዘግየት ተስማምታለች በሚል ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ በመስጠት የፕሮፓጋንዳ ትርፍ ለማግኘት ሙከራ ማድረጋቸውን ዋዜማ ያነጋገረቻቸው ሁለት የውጪ ጉዳይ ከፍተኛ ባላስልጣናት አረገግጠዋል።

የአፍሪቃ ህብረት በበኩሉ ባወጣው መግለጫ የግድቡን ሙሌት በተመለከተ ውይይት ስለመደረጉ ምንም አይነት አስተያየት አልሰጠም።

ለጉዳዩ ቅርብ የሆኑ የዲፕሎማቲክ ምንጮች እንደነገሩን ግብፅ በመንግስታቱ ድርጅት በኩል በአጋሮቿ ድጋፍ በኢትዮጵያ ላይ ጫና ለማሳደር ያደረገችው ሙከራ ባለፉት ቀናት ዉጤት ባለማምጣቱና ወደ አፍሪቃ ህብረት ሸምጋይነት እንዲሸጋገር በመወሰኑ የደረሰባትን የዲፕሎማሲ ኪሳራ ለማካካስ የተጠቀመችው የፕሮፓጋንዳ ስልት መሆኑን ያምናሉ።

የአፍሪቃ ሕብረቱ ድርድር ግብፅ በሙሉ ልብ የምትገባበት ባለመሆኑና በአጭር ቀናት ከስምምነት እንዲደረሰ ታስቦ የሚካሄድ ስለሆነ ውጤታማ ይሆናል የሚል ግምት እንደሌላቸው ከኢትዮጵያ ወገን የሆኑት ዲፕሎማት ያስረዳሉ።

ድርድሩ ወደ አፍሪቃ ህብረት መመለሱ ለሀገራችን ትልቅ የዲፕሎማሲ ስኬት መሆኑንና ከዚሀ ቀደም ወደ ሌሎች የድርድር መድረኮች በመሄድ የተከሰቱ ስህተቶ የታረሙበት እርምጃ ነው።

ይሁንና ግብፅ የአፍሪቃ ህብረት ድርድር እንዳይሳካ በማድረግ ጉዳዩ በድጋሚ ወደ ተባበሩት መንግስታት ድርጅት እንዲመለስ ፍላጎት ሊኖራት እንደሚችል ነግረውናል።

በኢትዮጵያ በኩል ካሉ ተደራዳሪዎች እንደሰማነው ደግሞ በሚቀጥሉት ቀናት የሚጀመረው ድርድር ከዚህ ቀደም መግባባት ባልተደረሰባቸውና የህግ ብያኔ ባልተሰጠባቸው ቅንፎች ላይ ያተኮረ እንደሚሆንና ለዚህም የተደራዳሪ ቡድኑ ዝግጅትና ምክክር ማድረጉን አስታውቀዋል።

Revelations
Senior Member+
Posts: 33672
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: የሕዳሴው ግድብ ቀጣይ የድርድር አጀንዳዎች [ዋዜማ ሬዲዮ]

Post by Revelations » 28 Jun 2020, 15:34

Please wait, video is loading...





Post Reply