ለማንኛውም የሚከተሉትን ድርጊቱንም በአጭሩ እንመርምር፡፡
1. ጠላቶቻችን በእምነት ሊያጣሉን እየተዘጋጁ ስለሆነ እንዘጋጅ ያለው የራሱን ፕላን በሌላ በማሳበብ ስለነበር እነሆ ዛሬ ላይ
እምነትን በእምነት ላይ ለማነሣሣት በጎንደርና በጎጃም መስጊድ ያቃጥላል፤ በኦሮሚያ/ፊንፊኔ ደግሞ ቤ/ክርስቲያን እንዲታወክ/
እንዲቃጠል በሰላዮቹ ያደርጋል፡፡
2. ኦሮሞን ለመከፋፈል ወለጋ ከሄድኩና ከገደሉኝ በማለት ዝባዝንኬ ዕቅዱን ቀድሞ ዘርዝሯል፡፡ ዛሬ ላይ ደግሞ ባሌ ሂዶ ደግሞ
አፋን ባሌ፣ አፋን ጉጂ እያለ ኦሮሞ ያለመሆኑን በራሱ ላይ እያሳበቀ አሮሞን ለመከፋፈል የሚንሊክን አስተምህሮ ያሰራጫል፡፡
የእኔ ጥያቄ የሕዝብ (በተለይ የቄሮ) ንቃተ-ሕሊና በደረሰበት ሁኔታ ይህ አይነት አካሄድ አብይን ሥልጣን ላይ ለማቆየትም ሆነ ኢትዮጵያ እንድትቀጥል ያግዝ ይሆን የሚለው ነው፡፡
Please wait, video is loading...