Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
QB
Member
Posts: 1934
Joined: 05 Dec 2012, 15:14

Tesfaye Gebreab gone mad. hahaha

Post by QB » 14 Jan 2020, 15:47

የተጎዳሁት እኔ ነኝ!











ትናንት በEmail የደረሰኝን (በእንግሊዝኛ ተጽፎ ወደ አማርኛ የተረጎምሁትን) ያልተጣራ አደገኛ መረጃ ስሜታዊ ሆኜ ወይም ደንግጬ ለጥቂት ሰአታት Post አድርጌው እንደነበር ይታወቃል።

እውነት ለመናገር ይበልጥ የተጎዳሁት እኔው ነኝ። ዞረም ቀረ Post ያደረግሁትን ደብዳቤ ወዲያውኑ ደምስሼዋለሁ።

ኦሮሞ ወዳጆቼ "Gadaa Gabra'ab እንዴት እንዲህ በፍጥነት ስሜታዊ ሆነ?" የሚል ጥያቄ ሲያነሱ - ሲጻፉ ውለዋል። "በለጸግህ እንዴ?" ብለው እኔን ከአብይ ጋር በማያያዝ ያላገጡብኝ ኦሮሞችም አሉ።

ከ"የቡርቃ ዝምታ" መታተም ጀምሮ ለ23 አመታት ከኦሮሞ ህዝብ ትግል ጋር የሚያውቁኝ አድናቂዎቼ የነበሩ ኦሮሞዎች ጭምር 180 ዲግሪ ተጠምዝዘው ሲያጠቁኝ አይቼ እንደተሳቀቅሁ አልደብቅም።

ርግጥ ነው፣ የዘመኑ ፋሽን እንዲያ ነው። ያም ሆኖ ኦቦ አዲሱ አረጋ በዚህ ፋሽን መሰረት ሲያጠቃኝ ከማንም ቀድሞ ፊትለፊት ወጥቶ ለኔ የተጋፈጠው ጃዋር መሃመድ ነበር። "ነባር ወዳጅህን ስለመጠበቅ" እንዲሁም "አዲስ ወዳጅ ለማፍራት ነባር ወዳጅህን መግደል እንደማይገባ" ህብረተሰብን ያስተማረው ጃዋር ነበር።

ስለኔ ማወራት ፈልጌ አይደለም። ርእሰ ጉዳዬ ስለ ጽናት ነው። ስለ እውነት ነው። "ገበሬው ማረሻውን ተክሎ ካልያዘ በሬዎቹ ይወዛወዛሉ።" የሚል አባባል አለ። እና እኔ በጭፍን የኦሮሞ መሪዎችን እንዳሞግስ ብቻ የምትጠብቁ ኦሮሞዎች ካላችሁ አልተግባባንም። እንደ አንድ የኦሮሞ ዜጋ ነጻ ነኝ። በሞጋሳ ባህል ያገኘሁትን ኦሮሞነት እንደ ጃኬት ከኔ ትከሻ ላይ የመግፈፍ መብት ያለው ኦሮሞ የለም። የምጽፈው ለኦሮሞ መራራ ቢሆን እንኩዋ መቃወም እና መሞገት እንጂ ሌላ አይቻልም። የማከበረው ኦቦ ዳውድ ኢብሳን እንኩዋ በጽሁፍ አፈር ድሜ ባበላው ለማንበብ ተዘጋጁ። ምክንያቱም ኦሮሙማ ይህን ይፈቅዳል። እኔ የማውቀው ኦሮሞነት እና ኦሮሙማ ከሙሉ ነጻነት ጋር ነው። "ኦሮሞ ኢትዮጵያን የሚመራበት ዘመን ከመጣ ተአምራዊ ዴሞክራሲ ያሳየናል" እያልኩ በስሜት ስጽፍ የኖርኩትም ለፕሮፓጋንዳ አልነበረም። የልቤን ነው።

አንድ ተጨማሪ እውነት ላንሳ!?

ትናንት Post ስላደረግሁት መረጃ መረዳት የምትችሉት ደብዳቤውን ማን እንደላከልኝ ብታውቁ ነበር። ዳሩ ግን ማንም ይሁን ማን ምንጊዜም ለወዳጆቼ ታማኝ መሆን ስላለብኝ ደብዳቤውን የላከልኝ ኦሮሞ ማን እንደሆነ ልነግራችሁ አልችልም። በርግጠኛነት የምነግራችሁ ገለልተኛ እና የተከበረ መሆኑን ብቻ ነው። ይህ ማለት ግን አይሳሳትም ማለት አይደለም። ተሳስቶ አሳስቶኝ ሊሆን ይችላል። ስሙን ብነግራችሁ ምናልባት እንደኔው ችግር ውስጥ ወይም የህሊና እስርቤት ውስጥ ልትገቡ በቻላችሁ። የሚሻለው እንደ ጥላሁን ገሰሰ አባባል "ሆድ ይፍጀው"፣ "ጊዜ ይፍጀው" ብሎ ሁሉን ለጊዜ መተው ነው።

ይችን አጋጣሚ በመጠቀም በእኔ ላይ ስም የማጠልሸት ስራ የጀመራችሁ "አዲሱ አረጋዎች" ሆይ! ይመቻችሁ!!


https://www.facebook.com/photo.php?fbid ... =3&theater

Zreal
Member
Posts: 486
Joined: 15 Mar 2019, 20:33

Re: Tesfaye Gebreab gone mad. hahaha

Post by Zreal » 14 Jan 2020, 19:50

lol we have it in text form or audio form. :lol: :lol: :lol:


Tesfaye Gebreab "አቢይ ለኦሮሞና ለኢትዮጵያ 'Necessary Evil' ነው።"

"አቢይ ለኦሮሞና ለኢትዮጵያ 'Necessary Evil' ነው።"

ዛሬ ማለዳ "ኦሮሚያ! - እንደ ደቡብ አፍሪቃ" በሚል ርእስ አንድ ጽሁፍ አስፍሬ ነበር።

ይዘቱ ባጭሩ "የዳውድ - መረራ ግንባር" በመጪው ምርጫ ኦሮሚያን ቢቆጣጠር በኦሮምያ የሚኖሩ ሌሎች ብሄሮችን እንደማይጎዳ፣ በግልባጩ ሁሉን አቅፎ ሊይዝ እንደሚችል የሚጠቁም በጎ የሚተነብይ ጽሁፍ ነበር።

ጽሁፉ በኔ FB ገጽ ከተሰራጨ ከሶስት ሰአታት በሁዋላ በኢሜይል አንድ አስደንጋጭ መልእክት ደረሰኝ።

በጣም በጣም የማከብረው፣ በሚዛናዊ አስተሳሰቡ ፍጹም የማልጠራጠረው ኦሮሞ ወዳጄ የሚከተለውን ደብዳቤ ላከልኝ።

"ለዳውድ - መረራ ግንባር ድልን የተመኘህበት ወይም የተነበይህበትን Post አይቼ ፈገግ አልሁ። 'ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው' የሚለው የአማሮች ተረት መጣብኝናም ትንሽ ተከዝሁ። 'አልሰሜን ግባ በለው' የሚለውንም አባባል ልትወስደው ትችላለህ። ዳውድ፣ በቀለና ጃዋር የወያኔ ባለሟሎች ሆነው መቅረታቸውን፣ የኦሮሞን ሕዝብ ትግል በገንዘብ መለወጣቸውን እያዘንሁ አረዳሃለሁ። እስከነችግሩ በአብይ ላይ ያነጣጠረ ቀስትህን አውርድ። አቢይ አሁን ለኦሮሞና ለኢትዮጵያ 'Necessary Evil' ነው።"

ይህን ደብዳቤ እንዳነበብኩ ቁጭ ባልኩበት ደነዘዝኩ። በመቀጠል በጣም ስሜታዊ ሆንኩ። ራሴን መቆጣጠር አልቻልኩም። በFB ግጽ ሰሞኑን ስጽፋቸው የነበሩትን ሁሉ ደመሰስኩ። ስልኬን ብሰባብረው ጭምር በወደድኩ።

ህሊናዬ መጣና ጮኸብኝ፣

"ለምን አርፈህ የስነጽሁፍ ስራህን አትሰራም? ውጣ ከፖለቲካ!!"

"ግለሰብ ነኝ። የኦሮሞ ማህበረሰብ አባል ነኝ። መሳተፍ መብቴ ነው!"

"ኦሮሞ አይደለህም። ራስህን አታታልል። ማንም አይቀበልህም።"

"ኦሮሞ ነኝ!"

"እሺ ይሁንልህ! ኦሮሞ ነህ እንበል! ግን በቃ ይቅርብህ። በዚህ ቀውጢ ጊዜ ዳር ቆመህ መታዘብ ይሻልሃል። የ31 አመታት ጥብቅ ኦሮሞ ወዳጅህ የጻፈልህን አየህ? አንተ ከሱ በላይ ኦሮሞ መሆን አትችልም። ከሱ በላይ ለኦሮሞ ልትቆረቆር አትችልም። ይሁን ቢባል እንኩዋ ጊዜው አደገኛ ነው። ከፖለቲካ ራቅ። ምናገባህ?"

"እና ምን ላድርግ?"

"FB ላይ መጻፍ አቁም።"

"መጻፍ ግን እፈልጋለሁ።"

"እንግዲያው ፖለቲካ ውስጥ አትግባ። ከፖለቲካ ውጭ የሆነ ወግ ብቻ ጻፍ። ፖለቲካውን ተው። ፈንጂ ነው። ቁስል ነው። አንተ ደግሞ ኤርትራዊ ነህ።"

ከ2020 ጀምሮ ቢራ መጠጣት አቁሜ ነበር። ባለፉት 12 ቀናት "ጠንቁዋዩ" ተብሎ በሚታወቀው ጥንታዊ የቻይና ስኒ እንኩዋ ቢራ እንዳልቀመስኩ በመሃላ ማረጋገጥ እችላለሁ። ዛሬ ግን ከመጠን በላይ ስለተረበሽኩ ራሴን ለማረጋጋት ወይም ድንጋጤዬን ለመበተን በሁለት ሰአታት ውስጥ አምስት የአስመራ ቢራ ቁዋ-ገጭ አደረግሁ።

ሞቅ ሲለኝ ድንጋጤዬ ለቀቀኝ።

መኪናዬን አስነስቼ ወደ መንደፈራ መንገድ ነዳሁ። በመጠጡ ሃይል ከተገቢው ፍጥነት በላይ መንዳቴ አልታወቀኝም። የሞተረኛ ትራፊክ ፖሊስ ከሁዋላ እንደሚከተለኝ ሳውቅ እየተበሳጨሁ ዳር ይዤ ቆምኩ።

ወረደ እና ሰላምታ ሰጠኝ።
እና ግን ወዲያው አወቀኝ።
በስሜት እንዲህ አለ።

"በቅርቡ ERI TV ላይ ቃለመጠይቅ ስትሰጥ ሰማሁህ። ጥሩ ነበር። በተለይ ስለ ኤርትራውያን ወጣቶች የተናገርከው በጣም ስቦኛል። አምላክ አሳብክን ያስምርልህ። ደህና ነህ ግን?"

ዘና አልኩ።
ከቅጣት መዳኔን አረጋገጥኩ። ትንፋሼ ቢለካ 1300 ናቅፋ እንደምቀጣ አውቅ ነበር።

ጥቂት ካወጋን በሁዋላ፣

"አነዳድህ ልክ አልነበረም።" አለኝ።

"ይቅርታ ተረብሼ ነበር።"

"ምነው በደህና? ምን ሆንክ?"

"ታሪኩ ረጅም ነው።"

"በል ረጋ ብለህ ንዳ! ለዛሬ አምልጠሃል።"

"አመሰግናለሁ ወንድሜ!"

እና ረጋ ብዬ እየነዳሁ ከአስመራ ከተማ ወጣሁ። በእርሻዎች መካከል ስደርስ መኪናዬን አቆምኩ እና ወረድኩ። አይኖቼ በሩቅ ያሉ ተራሮችን አዩ። ለጥ ባለው ሁዳድ ላይ አይኖቼን እስከ አድማስ ዘረጋሁ።

እናም እንዲህ ስል ጮህኩ፣

"ከቶ ሊሆን አይችልም!
በፍጹም! በፍጹም!!
በፍጹም ሊሆን አይችልም!!
በዚህ ወሳኝ ዘመን. . .
የኦሮሞ ህዝብ እየደገፋቸው. . .
የኦሮሞ የፖለቲካ ሃይሎች . . .
ከቶ ወደ ወያኔ ለመሄድ ለምን ይገደዳሉ?
ምን ለማግኘት?
ገንዘብ?
ጭንቅላት?
ህዝብ ብዛት?
ሁሉም አላቸው።
ሰው የሌለውን እንጂ ያለውን አይፈልግም!!
ከቶ ሊሆን አይችልም!!!
ኦሮሞ እንደ እፉኝት ልጆች አባት እና እናቱን አይገድልም!"

ይህን በጩኸት ስናገር በሩቅ እመለከታቸው የነበሩ የከበሳ ኤርትራ ተራሮችን ማየት አልቻልኩም። አይኔ ላይ ብዥ አለብኝ!!

https://www.facebook.com/photo.php?fbid ... =3&theater



QB
Member
Posts: 1934
Joined: 05 Dec 2012, 15:14

Re: Tesfaye Gebreab gone mad. hahaha

Post by QB » 15 Jan 2020, 14:43

Bizarre behavior is a classic sign of mental illness. He is having a mental breakdown :shock:




ሶስተኛው ቀለም!

ቀና ብዬ ሳየው የሰማዩ ቀለም ሰማያዊ ነበር። ምን ያህል እንደቆየሁ አላስታውስም። ግማሽ ሰአት ሊሆን ይችላል።

በድጋሚ ቀና ብዬ ሳየው የሰማዩ ቀለም ተቀይሮአል።

ለሶስተኛ ጊዜ ቀና ብዬ የሰማዩን ቀለም ማየት ፈራሁ። እናም አቀርቅሬ ወደ ጎጆዬ አዘገምኩ።

ቀና ብዬ ባላየውም የሰማዩ ቀለም ምን እንደሚመስል አውቄ ነበር!


Please wait, video is loading...

tlel
Member
Posts: 1559
Joined: 28 Dec 2019, 14:24

Re: Tesfaye Gebreab gone mad. hahaha

Post by tlel » 15 Jan 2020, 15:25

He doesn't love Oromo, under him he has eliminated many Oromos this is is not struggel he is Shabia /Tplf agent can't be Oromo lover there are many Mogassas too in Oromia what is the big deal? He is big deal. Oromon lib eyashebelele tikimun agendaw ezih lai derese. This is why, Tesfaye G/Ebab already knows the agenda of dr Aby when he said Aby le Oromo and Ethiopia is "necessary evil" Very scary! Does T g/ebab knows the agenda of Aby or was he trying to affect Aby so that Ethiopians be suspicious of him?

tlel
Member
Posts: 1559
Joined: 28 Dec 2019, 14:24

Re: Tesfaye Gebreab gone mad. hahaha

Post by tlel » 15 Jan 2020, 15:35

T G/Ebab knows how to write thanks to the Amharic language he took at H/Selassie University! He could be fabricating this fictional story in order to create rift among Oromos, Ethiopians, etc just like his fabricated Anole story

tlel
Member
Posts: 1559
Joined: 28 Dec 2019, 14:24

Re: Tesfaye Gebreab gone mad. hahaha

Post by tlel » 15 Jan 2020, 15:43

It is so sad, people just believe anything under the sun, they believe his story too and what he said is true, please G/Ebab eko fabricated a story! About Anole that never was the truth!

Tog Wajale
Member
Posts: 4918
Joined: 23 Dec 2017, 07:23

Re: Tesfaye Gebreab gone mad. hahaha

Post by Tog Wajale » 15 Jan 2020, 16:08


Post Reply