Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Abaymado
Member
Posts: 4208
Joined: 27 Sep 2017, 21:56

እስክንድር ነጋ በአገራችን እንደ ብርቅየው ዋልያ የታየ ድንቅ ሰው ነው : ግን አንዳንድ ስህተቶችን ማረም ያስፈልጋል

Post by Abaymado » 15 Dec 2019, 09:19

እስክንድር በመሀከላችን በመሆኑ በጣም ኩራት ይሰማኛል: ይህን የመሰለ ሰው ማገኘታችን እድለኞች ነን ማለት ይቻላል:: ምናልባትም እስክንድርን የሚያህል ሰው በአሁኑ ሰዓት ያላት አይመስለንም::
አንዳንዶች እስክንድርን ከማህተመ ጋንዲ ጋር ያመሳስሉታል:: ፅናቱ መቼም አስደማሚ ነው:: በቅርቡ በአገራችን በተነሳው ቀውስ እስክንድር ላይ የተደቀነው አደጋ ሁላችንንም አሳሥቦን ነበር:: ግን ነገሮች ወደ ጥሩ ሁናቴ እየተለወጠ ነው:: እስክንድር ከሀገር መውጣቱ ደሞ: ሕልውናውን እንዲያብብ አርጎታል:: እውቅና ካላቸው መንግሥታትና ድርጅቶች ጋር መገናኘቱ: የእሱን ተፈላጊነት ያሳየ እና ጥሩ ጥበቃና ክትትል እንዲደረግለት ያደረገ ነው:: ደፍረን በእስክንድር ላይ ያለው አደጋ ቀንሷል ማለት እንችላለን ::

ግን በጣም ሙገሳና ጭብጨባ በዛ :: እኛ አገር ዛሬ የተጨበጨበለት ነገ ስሙ በአሽሙር እንደሚነሳ እናቃለን:: እናም እስክንድር ይህን ከመጠን ያለፈ ሙገሳ እና ጭብጨባ ማስቆም ነበረበት: አሁንም ማረግ አለበት:: ይህ አጉል ሙገሳ የሚሰራውን ሥራ ሊያሰተጓጉል ይችላል::
እስክንድር የሰውን ሙገሳና ልገሳን ከቁም ነገር መቁጠር የለበትም::

እስክንድር አሁን ወደ አገር ቤት ተመልሶ ስራውን መስራት አለበት:: ባልደራስን ወደ ፓርቲ መቀየርና የአባላት ምዝገባ በሀገሪቱ ሁሉ ማድረግ አስፈላጊ ነው:: ይህ በጣም ወሳኝ ነው::