“የአሁኑ የኢሮብ አስተዳደር እንደ አዲግራት ከተማ ያሉ ታሪካዊ ይዞታዎቹን ተነጥቆ : ባሁኑ ወቅትም በአንዲት አነስተኛ ወረዳ ብቻ ይገኛል:: ‘ታሪካዊ ይዞታችን ተመልሶ በራስ የማስተዳደር መብት ይከበርልን ’ የሚለው ይፋዊ ጥያቄ ደግሞ የህዝባችንና የፓርትያችን እንቅስቃሴ ማጠንጠኛ ከሆነ ሰነባብቷል:: አሲምባ በጉዳዩ ላይ ትልቅ ውይይት ካደረገ በኃላ ጥያቄውን ወደ ፊት ማምጣትና በይፋ መጠየቅ እንዳለብን አምነናል:: ” ይላል የአሲምባ ፌስ ቡክ ገፅ :: ሲቀጥልም እንዲህ ይላል : “ከ 60 ኪሎሜትር በላይ ከእሮብ ህዝብ የተነጠቁ ታሪካዊ ይዞታዎቻችን ተመልሰው ‘የኢሮብ ልዩ ዞን አስተዳደር’ እንዲቋቋም በዛሬዋ ልዩ ቀን ለህወሓት ጥያቅያችንን እናቀርባለን:: ይቺም ቀንም የታሪክ መዝገብ ላይ ጉልህ ቦታ ይኖራታል:: ”
-
- Member
- Posts: 4214
- Joined: 27 Sep 2017, 21:56