Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Ejersa
Member
Posts: 3976
Joined: 05 Nov 2019, 10:39

ከህወሓቶች ጋር መቀመጥ በህዝብ ደም መቀለድ ነው!

Post by Ejersa » 03 Dec 2019, 19:51

በቀን 10/03/2012 ዓ.ም ተፅፎ በቁጥር 07642/2019 ወጪ የተደረገው አስገራሚ ደብዳቤ ይድረስ “ለህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ፣ መቀሌ” በማለት ይጀምራል። ጉዳዩ፡- “ስለተጠራንበት ስብሰባ ይመለከታል” በማለት ይቀጥላል። የዚህን ደብዳቤ ትርጉምና ፋይዳ በቅጡ ለመረዳት የተፃፈበትን አውድ በአጭሩ መዳሰስ ያስፈልጋል።

በደብዳቤው ላይ ፊርማቸውን አኑረው የላኩት የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ-አውጪ ግንባር (ኦብነግ) ዋና ሊቀመንበር አቶ አብዲርሃማን መሃመድ ናቸው። ከላይ እንደተገለፀው ዋና ጉዳዩ ሰሞኑን በመቀሌ ከተማ እየተካሄደ ባለው ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ከህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ለቀረበላቸው ጥሪ የተሰጠ ምላሽ ነው። ህወሓት በመቀሌው ስብሰባ ላይ እንዲገኙ ጥሪ ያቀረበላቸው በስልጣን ዘመኑ በአሸባሪነት የፈረጃቸው የኦብነግ አመራሮች ናቸው።

እንግዲህ በአከባቢው ያለውን የተፈጥሮ ነዳጅ አውጥቶ ለመሸጥ ሲል የኦጋዴን ህዝብን ከምድረገፅ ለማጥፋት ሲሰራ የነበረው፤ ለዚሁ ዓላማ አልሸባብ የተባለ ቡድንን ያደራጀው፣ በሶማሌላንድ በኩል የጦር መሳሪያ እያቀበለ በእጅ አዙር ሀገሩን ያስወረረው፣ የኢትዮጵያን ወታደሮችን ለሞት እየገበረ በፀረ-ሽብር ትግል ስም ከአሜሪካን እና እንግሊዝ ዶላር ሲቀበል፣ በሰላም አስከባሪ ስም ደግሞ ከተባበሩት መንግስታት ይቀፍል የነበረው ህወሓት…። ከቻይና የነዳጅ አፈላላጊ ድርጅት ጋር በመሆን የተፈጥሮ ነዳጅ ለማውጣት በኦጋዴ ህዝብ ላይ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ የፈፀመው፣ አብዲ ኢሌ የሚባል ንክ ከኤሌክትሪክ ፖል ላይ አውርዶ የሶማሌ ክልል ፕረዜዳንት አድርጎ የሾመው፣ የሶማሌ ህዝብን ለአስራ አምስት አመታት ያህል በመከላከያ ሰራዊት እና በሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል እንደ ጠላት እያደነ ሲያስገድል የነበረው፤ ንፁሃንን ማሰርና መግደል በውስጡ ያለውን ሰይጣናዊ መንፈስ ማርካት ተስኖት እስር ቤት ውስጥ ጅብና ነብር አስሮ ሲያሰቃይ የነበረው፣… ያለ ምንም ሃፍረት፣ ፀፀት፣ ይቅርታ፣ ተጠያቂነት፣… በጠራው ስብሰባ መገኘት የሶማሌን ህዝብ ማዋረድ ነው። የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ-አውጪ ግንባር ከህወሓት ለቀረበለት የስብሰባ ጥሪ የሰጠው ምላሽ ይህንን መራራ ሃቅ እንዲህ ሲል ገልፆታል፡-

ኦብነግ ከህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ ለቀረበለት የስብሰባ ጥሪ በሰጠው ምላሽ ሊሰመርባቸው የሚገቡ ሦስት መሰረታዊ ነጥቦች አሉ። የመጀመሪያው ህወሓት ላለፉት 27 አመታት በስልጣን ላይ በነበረበት ወቅት በንፁሃን ዜጎች ላይ ለፈጸመው ግፍና በደል ተጠያቂ ሊሆን ይገባል። ሁለተኛ በማንኛውም አግባብ ቢሆን ከህወሓት ጋር ትብብርና ጥምረት መፍጠር ላለፉት 27 አመታት ግፍና በደል በተፈፀመባቸው ዜጎች ደምና እምባ ላይ እንደመቀለድ ይቆጠራል። ሦስተኛ ከህወሓት ጋር በመተባበር የፌደራሊስቶች ግንባር ለመመስረት በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኙት ግለሰቦች እና ቡድኖች ህወሓቶች ቀድሞ በፈፀሙት እና ወደፊት በሚፈፀሙት የወንጀል ተግባር ላይ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ተሳታፊ እንደመሆናቸው መጠን ከተጠያቂነት አያመልጡም።

TGAA
Member+
Posts: 5626
Joined: 07 Apr 2019, 20:34

Re: ከህወሓቶች ጋር መቀመጥ በህዝብ ደም መቀለድ ነው!

Post by TGAA » 03 Dec 2019, 20:21

While the ONL makes clear and precise statement about the Ethiopian internal enemy #1 weyane , those who are intoxicated in their hate towards Amharas are more than willing to sleep with the murderous weyane that killed more then 6000 of Oromo-Ethiopians. Bekele gerba the most crud tribalist have made statement in Adama that the Oromo people are in debit to weyanes that couldn't never be repaid. Ayatola jawar has made statement that Oromos need to send a mediator to be under good grace of weyanes. We know now who stands for his people and who is against. The only reason the Oromo political prostitutes haven't flown to mekele in droves for the fake "federalist meeting" was a realization that the Oromo people would spite them out as a political entity for once and for all.

gagi
Member
Posts: 627
Joined: 16 Jun 2013, 16:34

Re: ከህወሓቶች ጋር መቀመጥ በህዝብ ደም መቀለድ ነው!

Post by gagi » 03 Dec 2019, 20:33

“ከህወሓት ጋር ትብብርና ጥምረት መፍጠር ላለፉት 27 አመታት ግፍና በደል በተፈፀመባቸው ዜጎች ደምና እምባ ላይ እንደመቀለድ ይቆጠራል”

This is the truth, and the whole TRUTH

Hallelujah, to the stride that the Ethiopian democratic forces are making! This is the final push to throw TPLF and the like-minded forces of evil to the dust bin of history!

Fed_Up
Senior Member+
Posts: 20631
Joined: 15 Apr 2009, 10:50

Re: ከህወሓቶች ጋር መቀመጥ በህዝብ ደም መቀለድ ነው!

Post by Fed_Up » 03 Dec 2019, 23:09

Who would forget this? Only ድምባዣም ህወሀት...

ማፈሪያዎች.. አይናችሁን በጨው አጥባችሁ ኑና አድኑን ብላችሁ ኦብነግን ስትጋብዙ ሸም የሚባል ነገር ስምታችሁ የምታቁ አትመስሉም::



^^^^ this is the barbaric TPLFISTS legacy which none of tplfists leader or followers will have a place today’s Ethiopia. Moreover, none of tplfists will have safe place in today’s Ethiopia. The rat’s hole of Mekele is the only warm place to tplfists to breath next day.

Game over#

I am just sayin

Fed_Up
Senior Member+
Posts: 20631
Joined: 15 Apr 2009, 10:50

Re: ከህወሓቶች ጋር መቀመጥ በህዝብ ደም መቀለድ ነው!

Post by Fed_Up » 03 Dec 2019, 23:19

Now the point is how the ኦብነግ and others respond to the invitation by the dead brain desperate agameWoch “Save me” party aka Tplf’s invitation?



I like that!!

Post Reply