እኔ የማዉቀው ለማ መገርሳ ኢትዮጵያዊ ስሜት የሌለዉ መሆኑን ነዉ!!!! ፕሬፌሰር መረራ ጉዲና
Posted: 01 Dec 2019, 14:45
“እኔ የማዉቀው ለማ መገርሳ ኢትዮጵያዊ ስሜት የሌለዉ
መሆኑን ነዉ፡፡ ይህን ያልኩበት ምክንያት ብዙ ነዉ፡፡ አንዱን
እንኳን ብጠቅስ” አሉ ፕሬፌሰር መረራ:-
“በ1997 ለማ መገርሳ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽነር
ነበር፡፡ ከዚያም ምርጫ ዘጠና ሰባት እንደተደረገ ፈልጎ መጣና አገኘኝ፡፡ ማስተርስ አስተምሬዋለሁ፡፡ ድግሪዉን ሲቪል ሰርቪስ ነዉ የተማረዉ፡፡ ባይሆን ሲቪል ሰርቪስ መማሩን አይናገርም እንጂ፡፡
ትንሽ ካወራኝ በኋላ ‘አባይ ጸሐዬና አቦይ ስብሃት ጋር ላስተዋውቅህ’ “ አለኝ፡፡ “እነ በረከት ስምኦን ጋር
እየተገናኘን አይደል እንዴ? ምን ይሆኑኛል? አልኩት እሱም
‘በረከትን ተወዉ እነሱ ጋር ላገናኝህ ላስተዋውቅህ’ አለኝ፡፡
አይ እኔ እነሱን ማግኘትም መተዋወቅም አልፈልግም ስለዉ
‘እሺ መለስ ጋር ላገናኝህ’ ይለኛል፡፡ እኔም በጀርባ ሄጄ
ማንንም ማግኘትና መተዋወቅ አልፈልግም ይልቁንስ
በምርጫዉ ምክንያት የተገደሉብንን ወደ 200 የሚሆኑ
አባላትና ደጋፊዎችን ጉዳይ አጣራልን አልኩት፡፡ እሱ
በሚያሳዝን ሁኔታ አይደለም 200 ሰዉ ይቅርና ሁለት መቶ ሺ
ሰዉም ያልቃታል እንጂ ለማንም የጎበና ፈረስ ኦሮሚያን
አናስረክብም፡፡ ማወቅ ያለብህ እኔና መለስ ዜናዊ ልዩነታችን
የብሔር ብቻ ነዉ አለኝ፡፡ በዚያዉ ተለያየን፡፡
እንግዲህ እሱ ትዉልድና እድገቱ ወደ ወለጋ ይጠጋል፤እኔን የሸዋ ሰዉ አድርጎ ነዉ የጎበና ፈረስ የሚለኝ፡፡ የአማራ ፈረስ ነህ እያለኝ ነዉ፡፡” ሌሎች አጋጣሚዎችና ምሳሌዎችንም ማንሳት እችላለሁ አሉ ፕሮፌሰር መረራ፡፡
“የሆኖ ሆኖ ለማ መገርሳ በፍጹም ኢትዮጵያ ስሜት የሌለዉ
ሰዉ ነዉ፡፡ በመሆኑም ኅሊናዬ የሚያዉቀው ኢትዮጵያዊ
አለመሆኑን ሳለ ሕዝቡ ደግሞ በተቃራኒዉ ሳያዉቀው
ወዶታል፡፡ ስለዚህ ሕዝቡን ከማስከፋም፣ ኅሊናዬንም
ከምሸዉድ መልኩ የኦሮሞ ይመስላል አልኩኝ፡፡ “
የለማ ሱስ ኢትዮጵያዊነትን መጥላት እንጂ መዉደድ
አይደለም፡፡ ለማ መገርሳ ሱሱ ማታለል ነዉ ለማለት ነዉ፡፡
ተራ አታላይነት፡፡ ለማ መገርሳ እና ዳዉድ ኢብሳ የአንድ
አካባቢ ሰዎች ናቸዉ፡፡ ሁለቱም ኢትዮጵያን የመጥላት ሱስ
ያናወዛቸዉ ናቸዉ፡፡ ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ነዉ በማታለልና
በማጭበረበር ቲም የመሰረቱት ..."