Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Revelations
Senior Member+
Posts: 33735
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

እውነታው ይኸው ነው -- ማለባበስ ይብቃ........!

Post by Revelations » 20 Nov 2019, 16:29

Please wait, video is loading...

Degnet
Senior Member+
Posts: 25078
Joined: 16 Feb 2013, 11:48

Re: እውነታው ይኸው ነው -- ማለባበስ ይብቃ........!

Post by Degnet » 20 Nov 2019, 16:46

Kemejemeria ezih tshuf endemilew anketeketognal ewnt senager ke Revelations yalegn alemewaded wede hual teche new ene zeregna aydelehum.Enezih kushashoch ahunm hagerachen beteley Tigray west endefelegachew eyetenageru alu.My life is my religion ke enezih yemigegn tekem gedel yegeb.Mecheresha selam ke Eritrea gar selam felagi Eritrawiann be medegef.Ignorance is our enemy,Motto.




Revelations
Senior Member+
Posts: 33735
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: እውነታው ይኸው ነው -- ማለባበስ ይብቃ........!

Post by Revelations » 21 Nov 2019, 14:13

Please wait, video is loading...


Ethoash
Senior Member+
Posts: 26144
Joined: 20 Apr 2013, 20:24

Re: እውነታው ይኸው ነው -- ማለባበስ ይብቃ........!

Post by Ethoash » 21 Nov 2019, 15:42



ይህንን የዘበኛ ካፖርት ማነው የገዛለት። አንደኛ በጣም ተልቆበታል ሁለተኛ ለምንድነው ቤትውስጥ ካፖርቱን ለብሶ መጥይቅ የሚያረገው።

Selam/
Senior Member
Posts: 11844
Joined: 04 Aug 2018, 13:15

Re: እውነታው ይኸው ነው -- ማለባበስ ይብቃ........!

Post by Selam/ » 21 Nov 2019, 17:09

Buda Woyane - ምን ኣገባህ ቆዳ ቢለብስ ? You seem to have a long experience in selecting security guard uniform. You‘re either a retired prison ዘበኛ or had been purchasing uniforms for TPLF torturers. IRIGUM!
Ethoash wrote:
21 Nov 2019, 15:42


ይህንን የዘበኛ ካፖርት ማነው የገዛለት። አንደኛ በጣም ተልቆበታል ሁለተኛ ለምንድነው ቤትውስጥ ካፖርቱን ለብሶ መጥይቅ የሚያረገው።


Revelations
Senior Member+
Posts: 33735
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: እውነታው ይኸው ነው -- ማለባበስ ይብቃ........!

Post by Revelations » 21 Nov 2019, 18:14

“እኛ የጃራ አባገዳ ልጆች ነን!” (ጀዋር በሚሊኒየም አዳራሽ የተናገረው፡)



“እኛ የጃራ አባገዳ ልጆች ነን!”
(ጀዋር በሚሊኒየም አዳራሽ የተናገረው፡ )
በያሬድ ይልማ
* …የአዲስ አበባ ከንቲባ እንዲሆን ህግ ከመሬት ተፈንቅሎ ተዘጋጅቶለት ፣ ወደ ስልጣል የመጣው ታከለ ኡማ ፣ በአዲስ አበባ የሚገኙትን የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መሬቶች በግማሹ እንዲወርሱም ጥሪውን አስተላልፏል!

በሐረርጌ ውስጥ በብዙ ስፍራዎች ፣ የኦነግ አስተሳሰብ ጠንሳሽ እና የክርስቲያን ዘር ኢትዮጵያ ውስጥ ለደቂቃ አይቶ መታገስ የማይችለው ነብሰ በላው ጃራ ፣ ስንት ክርስቲያን ኦሮሞዎችን ፣ ቄሶችን ፣ እንዲሁም የምኒሊክ ሰፋሪ የተባሉ ምስኪን ኢትዮጵያዊያንን ከዚሁ ከሐረርጌ ከተውጣጡ ፣ ሙስሊም የኦሮሞ ተወላጆችን ይዞ አሰቃቂ እልቂት እንደፈፀመ በሐረርጌ የኖረ ሰው በሙሉ የማይረሳው ነው፡፡ ብዙው ሰው የበደኖንና ፣ የአርባጉጉውን እልቂት ብቻ ነው የሚያስታውሰው፡፡
ታዲያ በውጪ ሐገር ሳለ አቶ ጀዋር መሐመድም ፣ የጥላቻ አባቱን ፣ የጃራን ፈለግ ተከትሎ ፣ ለክርስቲያኖች ያለውን ጥላቻ ፣ በአጠቃላይም ኢትዮጵያ የምትባለውን ሐገር ፣ በዚሁ የክርስትና እና የእስልምና እምነት አብሮ ፣ ተደባልቆ ፣ እንደ አንድ ሆኖ መኖርን ፣ “ሽርክ-ሀጥያት” አድርጎ እንደሚያየው ፣ አርኣያው ፣ ነብሰበላው ጃራ ፣ በተደጋጋሚ እንዴት እንደሚጠላ ፣ እንዴት በሜንጫ ፣ ክርስቲያኖችን አንገታቸው ላይ እንደሚል ፣ በገሃድ ሲናገር የኖረ በመሆኑ ፣ ዛሬ ድምፁን በዚህ ጉዳይ ላይ ሲቀንስ ሰዎች ፣ ቢረሱት አይፈረድባቸውም፡፡

እውነቱን ለመናገር ጀዋር ግን ለደቂቃ ያልተቀየረ ፣ የኢትዮጵያ የክርስቲያኑ ክፍል ፣ ለኦሮሞ የነፃነት ትግል ዋነኛ ችግር ነው ብሎ የሚያምን ፣ (ይህ ክርስቲያን ኦሮሞውንም ይጨምራል) ስለዚህም ከሁሉ አስቀድሞ በሚወደው እና በሚከተለው የነብሰበላው ጃራ አርኣያነት መሰረት ፣ ኦርቶዶክስ ከርስትናን ፣ መጀመሪያ ከኦሮምያ ፣ ከዚያም ከአጎራባች ስፍራዎች ማጥፋት ፣ የነብሱ ውጥን ናት፡፡ ለዚህም ነው ፣ ከአሜሪካ አቀባበል ተደርጎለት በሚሊኒየም አዳራሽ ፣ የማይረሳውን ነብሰበላ አባቱን በመፈክር “ እኛ የጃራ አባገዳ ልጆች ነን!” ብሎ ዛሬ ድረስ እሱንም የሚገፋውን ፣ ደም አፍሳሽ አረመኔ ሰው ስም የጠራው፡፡

ጀዋር መሐመድ ኢትዮጵያን መጥላት ብቻ ሳይሆን ክርስቲያን የሆነውን ክፍሏን ለማጥፋት ወስኖ ኢትዮጵያ የገባ መሆኑን ፣ ብዙ ሰዎች ከመጀመሪያው ጀምረን ስንናገር አልተቀበሉንም ነበር፡፡ ይህ ግልብ አይምሮ እና አስነዋሪነት ባንድ አጣምሮ ፣ ጃራን የሚያፈቅር ግለሰብ ፣ ዛሬ ደግሞ ሌላ እቅዱን በገሃድ አዲስ አበባ መሐል ቁጭ ብሎ ተናገረ፤ “ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አዲስአበባ የያዘችው መሬት ሰፊ ስለሆነ መነጠቅ አለባት ” ብሎ ተናገረ፡፡

እምነትአልባ የነበረው ኮሚኒስቱ ደርግ ፣ ካልጠፉ ቀናት እሮብ እና አርብ ላይ ህዝብ ስጋ እንዲበላ ሲያስገድድ የነበረው ደርግ እንኳ እጁን ያላነሳባትን እምነት እንዲሁም ህውሃት እንኳን ያልደፈሩትን አይነኬ የሆነውን የሀይማኖት ጉዳይ ውስጥ ዘሎ ገብቶ የጃራን የጦርነት አዋጅ አውጆ ጦርነቱን ለማስጀመር እየተዘጋጀ ነው።
ይህንን ሃሳቡንም እንዲያስፈፅሙለት ፣ የአዲስ አበባ ከንቲባ እንዲሆን ህግ ከመሬት ተፈንቅሎ ተዘጋጅቶለት ፣ ወደ ስልጣል የመጣው ታከለ ኡማ ፣ በአዲስ አበባ የሚገኙትን የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን መሬቶች በግማሹ እንዲወርሱም ጥሪውን አስተላልፏል፡፡ በነብሰ በላው ጃራ መንፈስ የሚነዳው ፣ ጀዋር ይህ በኢትዮጵያ ምድር ገብቶ በሐይማኖት ጉዳይ ላይ ፣ የፖለቲካ ጦርነት ያወጀበት የመጀመሪያው አዋጅ ነው ልብ በሉ፤ ይህ እንግዲህ የት እንደሚያደርሰው አብረን የምናየው ይሆናል፡፡

Post Reply