Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Ejersa
Member
Posts: 3976
Joined: 05 Nov 2019, 10:39

ኢህአዴግን ህብረ ብሔራዊ ፓርቲ ለማድረግ የተካሄደው የዝግጅት ሥራ መጠናቀቁ ተገለጸ!

Post by Ejersa » 13 Nov 2019, 12:49

ኢህአዴግን አጋር ድርጅቶቹን በማካተት ህብረ ብሔራዊ ፓርቲ ለማድረግ የተካሄደው ዝግጅት መጠናቀቁን የኢህአዴግ ምክር ቤት አስታወቀ።

የግንባሩ አባላት፣ ሕዝቡና የመንግስት ሠራተኛው ለውህደቱ ተግባራዊነት የማይተካ ሚናቸውን እንዲወጡ ምክር ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።

የኢትዮጵያ አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር /ኢህአዴግ/ ላለፉት 29 ዓመታት ከአራት ፓርቲዎች ጋር ግንባር ፈጥሮ ሀገሪቱን ሲመራ መቆየቱ ይታወሳል።

በሀገሪቱ ባለፉት ሁለት ዓመታት በተካሄደው ሕዝባዊ እምቢተኝነት በመጣው ለውጥ አማካኝነት ግንባሩን ወደሀገራዊ ህብረ ብሔራዊ ፓርቲነት ለማምጣት በግንባሩ ጽሕፈት ቤት በኩል የዝግጅት ሥራ ሲያከናውን ቆይቷል።

ውህደቱን ከግንባሩ አባል ድርጅቶች ባሻገር ላለፉት ዓመታት ከግንባሩ ጋር በአጋርነት ሲሰሩ የቆዩትንም ሌሎች ፓርቲዎች የሚያካትት መሆኑም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የውህደቱን የዝግጅት ሥራ አስመልክቶ የግንባሩ ምክር ቤት ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መለሰ አለሙን አነጋግሯል።

አቶ መለስ አለሙ የኢህአዴግን የውህደት ሂደት አመጣጥን የሚገልጹት የሕዝብን የመለወጥ ፍላጎትና የልማት ጥያቄን ከመመለስ አኳያ ነው።

ውህደቱ ሕዝባዊ መሠረት የሌለው ነው በሚል በአንዳንድ አካላት የሚቀርበውን አስተያየት አቶ መለስ አይቀበሉትም።

እነዚህ አካላት ለውጡ እንዳይመጣ በየጊዜው መሰናክል ሲያስቀምጡ የቆዩ ናቸው የሚሉት የጽሕፈት ቤት ኃላፊ፤ የውህደቱ አስፈላጊነት ከድርጅቱ 5ኛ ጉባኤ ጀምሮ ሲታሰብበት የመጣ አቋም መሆኑን ያብራራሉ።

የድርጅቱ ውህድ መሆን የሀገር መሠረታዊ አንድነትን በመፍጠር በጋራ መልማትን ከማምጣት ባለፈ አባላቱ በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ወጥ አቋምና አስተሳሰብ እንዲኖራቸው እንደሚያስችልም አቶ መለስ አለሙ ያስረዳሉ።

የኢህአዴግ አባልና አጋር ድርጅቶችን በማዋሀድ ሀገራዊ ራእይ ያለው ፓርቲ የመፍጠሩ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን አቶ መለሰ ያብራራሉ።

በመሆኑም ለሚፈጠረው ሀገራዊ ፓርቲ እውን መሆን የግንባሩ አባላት፣ የመንግሥት ሠራተኛውና ሕዝቡ እንደወትሮ ሁሉ ገንቢ ሚናቸውን እንዲወጡ ኃላፊው ጥሪ አቅርበዋል።

ውህደቱ ከሕወሓት በቀር በሌሎቹ የግንባሩ አባላት ይሁንታ ማግኘቱን የብሔራዊ ድርጅቶቹ አመራሮች በመገናኛ ብዙሃን መግለጻቸው ይታወቃል።

እንደኢዜአ ዘገባ በዚህ ሳምንት የሚካሄደው የግንባሩ የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ላይ የውህደቱ ጉዳይ ዋና አጀንዳ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል።
****
ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ

Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4080
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

Re: ኢህአዴግን ህብረ ብሔራዊ ፓርቲ ለማድረግ የተካሄደው የዝግጅት ሥራ መጠናቀቁ ተገለጸ!

Post by Za-Ilmaknun » 13 Nov 2019, 13:29

This is what TPLF has to say through its mouth piece Aiga forum about the ongoing revamping of EPRDF party as has been expected:


"EPRDF is Done and TPLF is Looking Ahead for a New Begining.
According to a reliable source, the dying EPRDF is planning to hold an executive meeting within days. A reliable source has confirmed to us PM Abiy is trying to salvage the dying front without TPLF. As you all know EPRDF as a front has been near death for a while! Abiy has been trying to form a new unitary/prosperity party without success until now.

According to our source, TPLF is ready to move on and forge a new partnership with federalist parties that respect the constitution and the rights of nations and nationalities. The road ahead is full of uncertainty but TPLF is ready to play its role in clearing the road for a new beginning in Ethiopian politics.

Our source told us the new proposed party and TPLF have two opposed political programs and there is no plan to join any sham meetings going forward. The only meeting it will attend is to finalize the breakup! Aigaforum Nov 13, 2019"

Ejersa
Member
Posts: 3976
Joined: 05 Nov 2019, 10:39

Re: ኢህአዴግን ህብረ ብሔራዊ ፓርቲ ለማድረግ የተካሄደው የዝግጅት ሥራ መጠናቀቁ ተገለጸ!

Post by Ejersa » 13 Nov 2019, 13:32

:lol: :lol: :lol: :lol:
Za-Ilmaknun wrote:
13 Nov 2019, 13:29
This is what TPLF has to say through its mouth piece Aiga forum about the ongoing revamping of EPRDF party as has been expected:


"EPRDF is Done and TPLF is Looking Ahead for a New Begining.
According to a reliable source, the dying EPRDF is planning to hold an executive meeting within days. A reliable source has confirmed to us PM Abiy is trying to salvage the dying front without TPLF. As you all know EPRDF as a front has been near death for a while! Abiy has been trying to form a new unitary/prosperity party without success until now.

According to our source, TPLF is ready to move on and forge a new partnership with federalist parties that respect the constitution and the rights of nations and nationalities. The road ahead is full of uncertainty but TPLF is ready to play its role in clearing the road for a new beginning in Ethiopian politics.

Our source told us the new proposed party and TPLF have two opposed political programs and there is no plan to join any sham meetings going forward. The only meeting it will attend is to finalize the breakup! Aigaforum Nov 13, 2019"

Post Reply