Page 1 of 1

የወያኔ ፌዴራሊዝም ትልቋን ኢትዮጵያ የምትባለዋን ዶሮ አንስተህ ፉርኖ ውስጥ አስገብተህ ቀልታ ስትወጣ የሚጣፍጠውን እኔ እበላለሁ፤ ሌላህ ግን ልፋጭ ብላ ያለ ስርዓት ነው

Posted: 07 Nov 2019, 19:29
by Ejersa
የወያኔ ፌዴራሊዝም ትልቋን ኢትዮጵያ የምትባለዋን ዶሮ አንስተህ ፉርኖ ውስጥ አስገብተህ ቀልታ ስትወጣ የሚጣፍጠውን እኔ እበላለሁ፤ ሌላህ ግን ልፋጭ ብላ ያለ ስርዓት ነው፡፡ ስም ሰጡት ግን Modern ስም ፌዴራሊዝም አሉት፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ግን ፌዴራሊዝም አልነበረም፤ ከአሁን ወዲያ ነው ፌዴራሊዝም መገንባት የምንችለው፡፡ የሚገርምሽ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን የሚል ሌላ ነገር አስቀመጡ አጠገቡ፤ እርሱ ቁጭ ብሎ ሌላው አማራውም የሀገር ልብሱን፣ አፋሩም የሀገር ልብሱን፣ ሶማሌውም ደቡቡም ኦሮሞውም የሀገር ልብሱን ለብሶ ይጨፍርለታል እርሱ እንደፈረንጅ colonialist ቁጭ ብሎ ይመለከታል (ይዝናናል)፡፡ፕ/ር መሀመድ ሐሰን የሶማሌ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አማካሪ