Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Abaymado
Member
Posts: 4214
Joined: 27 Sep 2017, 21:56

በዓመት 80,000 የሶማልያ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ! የአባይ ግድብ ከ16 ተርባይነሮች ሁለቱን ለመቀነስ መወሰኑ

Post by Abaymado » 20 Sep 2019, 12:04


ሶማልያ ውስጥ ባለው ድርቅና የፀጥታ ምክንያት ወደ 80,000 የሶማልያ ስደተኞች ኢትዮጵያ እንደሚሰደዱ ተገልፅዋል::
መንግስት ብታስብበት ጥሩ ነው:: ለግብፅ በምንም ተአምር አንተኛም!! ጠላታችን ብቻ ይህን ያረገዋል::
የሕዳሴው ግድብ የተርባይኖች ቁጥር እንዲቀነስ ተወሰነ



የሕዳሴው ግድብ የተርባይኖች ቁጥር እንዲቀነስ ተወሰነ
September 20, 2019 0

ዋዜማ ራዲዮ- የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ዲዛይን የተሰራው 16 የሀይል ማመንጫ ተርባይኖች እንዲኖሩት ታስቦ መሆኑ የሚታወስ ነው። እነዚህ 16 የሀይል ማመንጫ ተርባይኖች በተለያየ ጊዜ በተሰሩ የጥናት ማሻሻያዎች ከህዳሴው ግድብ የሚያመነጩት ሀይል 6450 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ሀይል ይሆናል ተብሏል። የተርባይኖች ምርትና ተከላ ስራ ላይ የብረታብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን ድርሻ ሙሉ ተቀምቶ ሙሉ ስራው ለውጭ ኩባንያዎች መሰጠቱ የሚታወቅ ነው።
ዋዜማ ራዲዮ ያገኘችው መረጃ እንደሚያሳየው አሁን ላይ ለታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ይገጠማሉ ተብሎ ከነበሩት 16 የሀይል ማመንጫ ተርባይኖች ውስጥ ሁለቱ እንዲቀሩ ተወስኗል። ግድቡ አስራ አራት ተርባይኖች ብቻ እንዲኖሩት የሚያስችል የዕቅድ ክለሳ እንዲደረግ በከፍተኛ የመንግስት አካላት ውሳኔ መተላለፉን ስምተናል።
ለመሆኑ እንዲህ አይነት ውሳኔ መወሰኑ ግድቡ በሚያስገኘው ጥቅምና ጉዳት ላይ የሚያመጣው ተጽእኖ ምንድነው? የሚል ጥያቄ ዋዜማ ራዲዮ አቅርባ ምላሽን አግኝታለች። በመጀመርያ የግድቡ የሲቪል ስራ ሲከናወን 16 የሀይል ማመንጫ ተርባይኖችን ገጥሞ ሀይል ለማመንጨት በመሆኑ ለእያንዳንዱ ተርባይን ማስቀመጫ የሚሆን ግንባታ ወጪ ወጥቶ በግድቡ ላይ ተከናውኗል ። ሁለቱ የሀይል ማመንጫ ተርባይኖች የማይገጠሙ ከሆነ ሁለቱን ሀይል ማመንጫዎች ማስቀመጫ ለመስራት የወጣው ወጭ እንደኪሳራ የሚታሰብ ይሆናል።
የህዳሴው ግድብ 6450 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ሀይልን ያመነጫል እንደመባሉ ይተከላሉ ተብሎ ለነበሩት 16 ተርባይኖች ተካፍሎ የሚመረት ሀይል ነው የሚል ግንዛቤ አለ። የዋዜማ ምንጭ እንዳሉን ከሆነ ግን የተርባይን ቁጥር መቀነስ ግድቡ 6450 ሜጋ ዋትን እንዳያመነጭ የሚያደርግ ሳይንሳዊ ምክንያት የለም። ግድቡ በ10 የሀይል ማመንጫ ተርባይኖችም በቂ ውሃ እስካለ ድረስ 6450 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክን ማመንጨት ይችላል።
አሁን የሀይል ማመንጫ ተርባይኖች ቁጥር እንዲቀንስ የሚያደርጉ ውሳኔዎች የሚያመጡት ጉዳት ቢኖር አንዱ ከፍተኛ መጠን ያለው ውሀ በግድቡ ውስጥ በሚገባበት ጊዜ ውሀውን በከፍተኛ መጠን ተጠቅሞ ከፍተኛ መጠን ያለው ሀይል የማመንጨት እድልን ማሳጣት ነው።ለዚህ ሲባል የተርባይኖች ቁጥር ከፍ ቢል ይመረጣል።በሌላ በኩል የተቀነሱት ተርባይኖች ይተከላሉ በሚል ለግንባታ የወጣው ወጭ ኪሳራ ነው።
የህዳሴው ግድብ 16 የሀይል ማመንጫ ተርባይኖች ስላሉት 6450 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ያመነጫል ማለት አይደለም ይላሉ የዋዜማ ራዲዮ ምንጭ። አሁን ባለ የአየር ንብረት ሁኔታ ከቀጠለ ግድቡ በ16 የሀይል ማመንጫዎችም በሙሉ አቅሙ ሀይል የማመንጨት ስራ ሊሰራ የሚችለው በአመት ውስጥ ለአራት ወራት ብቻ ነው። ይህም የሚሆነው በውሀ አቅርቦት ምክንያት ነው። ከግድቡ የሀይል ማመንጫ ጋር የሚያያዘው ዋናው ጉዳይ የውሀ ጉዳይ ሲሆን በአካባቢ ጥበቃም ሆነ በዲፕሎማሲው መሰራት ያለበት እዚሁ ላይ ነው ተብሏል።
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የሚደረጉ ይህ አይነት ማሻሻያዎች ዲፕሎማሲያዊ እይታቸው ምንድነው ? የሚል ጥያቄ ማስነሳቱም አይቀርም።በዚህ ዙርያ ያነጋገርናቸው ባለሙያ እንዳሉን የተርባይኖች ቁጥር መቀነስ የህዳሴው ግድብ ላይ ከሚያመጣው ተጽእኖ በላይ የግብጽ መንግስት ግድቡን አስመልክቶ የሀገሬን ጥቅም አስከብሬያለሁ በሚል ፖለቲካ ሊገዛበት ይችላል።
በጉዳዩ ላይ የውሀ የመስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር ምላሽ እንዲሰጠን ብንጠይቅም እስካሁን ምላሽ አላገኘንም። [ዋዜማ ራዲዮ]


http://wazemaradio.com/%E1%8B%A8%E1%88% ... %E1%8B%B2/
ምንጭ : ዋዜማ ሬድዮ

simbe11
Member
Posts: 2087
Joined: 23 Feb 2013, 13:02
Location: Addis Ababa

Re: በዓመት 80,000 የሶማልያ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ! የአባይ ግድብ ከ16 ተርባይነሮች ሁለቱን ለመቀነስ መወሰኑ

Post by simbe11 » 20 Sep 2019, 12:18

"በዓመት 80,000 የሶማልያ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ"

About a million Ethiopians flood from their country, destination unknown.
Sad!!!

simbe11
Member
Posts: 2087
Joined: 23 Feb 2013, 13:02
Location: Addis Ababa

Re: በዓመት 80,000 የሶማልያ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ! የአባይ ግድብ ከ16 ተርባይነሮች ሁለቱን ለመቀነስ መወሰኑ

Post by simbe11 » 25 Sep 2019, 12:09

As per your definition, Ethiopia is where refuges come to, not people running away from. But, the Afar and the Arabian deserts are telling us a different story. I urge you to travel to Afar or Djibouti and see how many Ethiopians are desperately waiting for their dinghy ride to the Arabian countries.
present wrote:
20 Sep 2019, 18:37
How about your Ascari sisters begging on the streets of Addis? You don't want to talk about them? :lol:


simbe11 wrote:
20 Sep 2019, 12:18
"በዓመት 80,000 የሶማልያ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ"

About a million Ethiopians flood from their country, destination unknown.
Sad!!!

simbe11
Member
Posts: 2087
Joined: 23 Feb 2013, 13:02
Location: Addis Ababa

Re: በዓመት 80,000 የሶማልያ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ! የአባይ ግድብ ከ16 ተርባይነሮች ሁለቱን ለመቀነስ መወሰኑ

Post by simbe11 » 25 Sep 2019, 13:31

Stop by Dubai Airport and sea Ethiopians begging the Arabs.
I am just telling you not to brag.
present wrote:
25 Sep 2019, 13:25
Ascari :lol:

What is this has to do with ascari Eritrean begging on the streets of Addis? :lol:
simbe11 wrote:
25 Sep 2019, 12:09
As per your definition, Ethiopia is where refuges come to, not people running away from. But, the Afar and the Arabian deserts are telling us a different story. I urge you to travel to Afar or Djibouti and see how many Ethiopians are desperately waiting for their dinghy ride to the Arabian countries.
present wrote:
20 Sep 2019, 18:37
How about your Ascari sisters begging on the streets of Addis? You don't want to talk about them? :lol:


simbe11 wrote:
20 Sep 2019, 12:18
"በዓመት 80,000 የሶማልያ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ"

About a million Ethiopians flood from their country, destination unknown.
Sad!!!

simbe11
Member
Posts: 2087
Joined: 23 Feb 2013, 13:02
Location: Addis Ababa

Re: በዓመት 80,000 የሶማልያ ስደተኞች ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ! የአባይ ግድብ ከ16 ተርባይነሮች ሁለቱን ለመቀነስ መወሰኑ

Post by simbe11 » 26 Sep 2019, 10:48

Makes no sense. As we all know central Piassa is filled with beggars and all the stop lights got at least a few knocking on your window.
It was all happening long before the borders are opened up. Ain't saying you are lying,because I don't know, but you are exaggerating it.
ደሞ ለልመና ማን ........
present wrote:
25 Sep 2019, 21:47
Are you stupi'd or what? ascaris are there too.

Again, What does it has to do with Ascari Eritreans begging on the streets of Addis? :lol: :lol: :lol:

Post Reply