Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum

mitmitaye
Member
Posts: 680
Joined: 29 Mar 2018, 15:18

Re: በጉራጌዎች ዘንድ የገዳ ስርአት ስለመኖሩ አላውቅም - ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ

Post by mitmitaye » 03 Sep 2019, 12:49

Most southern ethnics of Ethiopia had gada system. Actually, oromos learned the gada system from the sidamas and added their warring culture to it.

Gada is not oromo culture.

Horus
Senior Member+
Posts: 30915
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: በጉራጌዎች ዘንድ የገዳ ስርአት ስለመኖሩ አላውቅም - ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ

Post by Horus » 03 Sep 2019, 13:28

ፍቅሬ ቶሎሳ እንደ ወትሮው በውል ባላጠናው ነገር ላይ ሃሳብ ወረወረ ። ሲማ፣ ጋሪ የሚባል ስም ሶዶ አካባቢ ያሉት ክስታኔዎች ስለ ሚጠቀሙ ገዳ ሊኖር ይችላል አለ።

አንደኛ ፍቅሬ ሲማ እና ጋሪ የሚሉት ቃላት የሴም ቃላት እንደ ሆኑ ኤቲሞሎጂውን አያቅም ። ክስታኔውዎች ሲማ ይላሉ፣ ስሜ፣ ሲሜ ይላሉ ። ስም የሚለው የሴም ቃል ነው። ትርጉሙ መሰሌ፣ መሳዬ፣ ማለት ነው ።

ጋሪ የሚለው ከግብጽ ተነስቶ እስከ ግሪክ፣ እስከ ላቲን እስከ ሴም ድረስ ያለው ጉራጌ ኬር የሚለውና የጉራጌ ኮስሞሎጂ መሰረት የሆነው ቃል ነው። ኬር ማለት በኦሪት ዘመን የነበረውን ትርጉም እንኳ ብንተው ዛሬ በጉራጌ ዘንድ ሰላም፣ ሙሉ፣ ለም፣ ደህና፣ ጤና፣ የተባረከ፣ ሌላም ሌላም የሚል እጅግ ከፍተኛ ጽንስ ነው። ጉራጌ እዝጌር ይላል። እዝኬር ማለት ነው። ለጉራጌ እግዚአብሄር ከሚለው ቅዱስ ቃል ቀጥሎ ያለው ክቡር ቃል ኬር ነው። በእግዚአብሄር ስም ወስጥ ሄር የሚለው ኬር ነው። ያ ነው የጋሪ ግንድ። ኦሮሞ ነው ኬርን ከጉራጌ ተውሶ ጋሪ ያለው። ዛሬ ጂዳ ተብለው ስለ ገዳ ሚቀባጥሩት ግማሽ ክስታኔ ግማሽ ኦሮሞች በክስታኔውች ዘንድ ላሊጌ ወይም ሰሜንጌ ይሏቸዋል። ድሮ ራሳቸውን ክስታኔ ብለው ቋንቋውን ሲናገሩ ነበር። ኦነግ አዲሳባ ሲገባ ስልጣን ፍለጋ ኦሮሞ ነኝ አሉ ። አሁን ግራ ስለተጋቡ ገዳን ከጉራጌ ጋር አያይዘው የቀባጥራሉ።

የክስታኔ ግንድ እና ጥንታዊ ስሙ አይመለል ነው ። አይመለል ማለት አማኝ ማለት ነው። በዚያም ሳቢያ ነው ክስታኔ (ክርስቲያን) የሚለውን ስም የያዙት ።

የክስታኔ ማህበራዊ፣ ህጋዊና እና አስተዳደር ስርአት ጎርደና ወይም የጎርደና ሴራ ይባላል። ሴራ ማለት ስርአት ለሚለው ግዕዝ ነጠላ ቃል ነው። (ሴራ፣ ስርአት) ። ድርድሮ በአማርኛ ጎርደማም ይባል ነበር ። ጎርደና እጅግ ጥንታዊ ሰር አለው። ከኦሪታዊ እምነትና የቃል ኪዳን ሰራት ጋር ይያያዛል። ዛሬ የቃሉ ትርጉም ያገር ጉባኤ፣ ያገር ፓርላማ ማለትና ያገሩ ከፍተኛ ስልጣን ነው። ክስታኔ ሆነ ሌሎቹ የጉራጌ ወገኖች በገዳ የተወረሩ እንጂ በገዳ ራሳቸውን ያደራጁ አይደሉም ። ሰባት ቤት የራሱ የጆካ እና ቅጫ (መቀጫ) አለው። መስቃን ሂዱ ያው ነው ። ወዘተ

ኦሮሞ በጉራጌ ላይ የሚቃዥውን አዲስ የወረራ ህልም ያቁም !!!

Horus
Senior Member+
Posts: 30915
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: በጉራጌዎች ዘንድ የገዳ ስርአት ስለመኖሩ አላውቅም - ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ

Post by Horus » 03 Sep 2019, 14:10

ፍቅሬ ቶሎሳ ተምሮ ተምሮ ወደ ኋላ ተምልሶ በተረት ሚትዝ ቆሞ ትውልድ እያደናገረ ያለ ሰው ነው። እሱ ግዚውን ወስዶ ያንድ ቃል ስርና ስነት (ፊሎሎጂ እና ኤቲሚሎጂ) የማያተጠና በመሰለው ሃሳብ እየወረወረ ምሁራዊ ዝቅጠት ወርዷል። አንድ ሰው አንድ ቃል ስላለ ወይ ያ ስም አርጎ ስለያዘ በዚያ ብቻ ቆሞ መደምደም እንኳን ከፒኤች ዲ ካልተማረ አይጠበቅም ።

Horus
Senior Member+
Posts: 30915
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: በጉራጌዎች ዘንድ የገዳ ስርአት ስለመኖሩ አላውቅም - ፕ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ

Post by Horus » 03 Sep 2019, 14:25

በነገራችህን ላይ ዛሬ ከግዜ ብዛት ክስታኔዎች ጎርደና የሚለውን ቃል ትርጉም እንደ ሜታፎር የቤት ግድግዳ እንጨት ማለት ነው ይላሉ። ትክክለኛ ትርጉሙ ግ ን ያገር ዳኛ፣ ያገር መዳኛ፣ ያገር ጉባኤ ማለት ነው። በ17ኛው ዘመን ጉራጌው ራስ ዘስላሴ ያጉራ ጠነ ይሉት የነበረው ነው። ጠነ ማለት ሃይል፣ ስልጣን ማለት ነው። ራሱ ስልጣን የሊለው ቃል ውዚያ አለ ። አጉራ፣ ጎራ፣ ጎር ማለት አገር ማለት ነው። ስለዚህ ጎርደና ማለት ያገር ባለስልጣን ያገር አስተዳደር ማለት ነው።

የስር አቱ ዝርዝር እዚህ በዘብዘብ አይሻም ። ይህ ነው በዘልማድ የሶዶ ጉራጌ የሚባሉት የክስታኔ ህዝብ ስርአት ።

Post Reply