1. በምዕራብ ሐረርጌ በርደዴ በተባለ ቦታ፣ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት 10 ሰዎች መሞታቸውን ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ዘግቧል፡፡ 3 ሰዎችም ቆስለዋል፡፡ በግጭቱ ሳቢያ መኪና መንገዶች በመዘጋታቸው፣ ከሐረር-አዳማ-አዲስ አበባ የሚጓዙ መንገደኞች በረሃ ላይ እንደቆሙ ናቸው፡፡ አዲስ ስታንዳርድ በበኩሉ የኦሮሚያ ኮምኒኬሽን ቢሮን ጠቅሶ እንደዘገበው፣ ግድያውን የፈጸሙት ታጣቂዎች ናቸው፡፡ ጥቃቱን ተከትሎም የመከላከያ ሠራዊት አባላትና ፖሊሶች ወዳካባቢው ገብተዋል ተብሏል፡፡ የጥቃቱ አድራሾች ማንነት አልተገለጸም፡፡
-
- Senior Member+
- Posts: 33674
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
-
- Senior Member+
- Posts: 33674
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
-
- Senior Member+
- Posts: 33674
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: ኦነግ በምእራብ ሃረርጌ ጥቃት አደረሰ ፣ ኦህዴድ/ኦዲፒ አጥቂን በስሙ መጥራት ፈርቷል
-
- Senior Member+
- Posts: 33674
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: ኦነግ በምእራብ ሃረርጌ ጥቃት አደረሰ ፣ ኦህዴድ/ኦዲፒ አጥቂን በስሙ መጥራት ፈርቷል
ከሀረር ወደ ኢዲስ አበባ በሚወስደው መንገድ ልዩ ስሙ ቦርደዴ አካባቢ በተፈጠረ ግጭት ሰባት ሰዎች መሞታቸው ተገለጸ።
አማራ ሚድያ ማዕከል/አሚማ
ነሃሴ 2 ቀን 2011 ዓ.ም አዲስ አበባ ሸዋ
የአካባቢው ነዋሪዎች ግጭት መፈጠሩን አሩጋግጠውልናል ብሎ ኢትዮ ኤፍ ኤም እንደዘገበው በግጭቱ 7 ሰዎች ሞተዋል፤ 3 ሰዎች ደግሞ በህይወት እና በሞት መካከል ናቸው፡፡
የሚመለከተው አካል ጉዳዩን አጣርቶ መፍትሄ እንዲሰጣቸውና የተፈጠረውን ችግር እንዲያስረዳቸውም ነዋሪዎቹ ጠይቀዋል፡፡
በአካባቢው በተፈጠረው ግጭት መንገዱ በመዘጋቱ ምክንያት ምንም ዓይነት መኪና እንዳያልፍ ተዘግቷል፡፡
ከሀረር ወደ አዲስ አበባ፣ ናዝሬት እንዲሁም ሌሎች አካቢዎች ለመሄድ የተሳፈሩ ተጓዦች ከማለዳው 2 ሰዓት ጀምሮ መንገዱ መዘጋቱን እና በረሀ ላይ መሆናቸውንና መንቀሳቀስም እንዳልቻሉ ታውቋል፡፡
ከቦርደዴ - አዋሽ መግቢያ ድረስ መኪኖች መንቀሳቀስ ባለመቻለቸው ተሰልፈው መቆማቸውን እና ይህ ነው ብሎ የተፈጠረውን ችግር ያስረዳቸውም ሆነ መፍትሄ የነገራቸው አካል እንደሌለ ተናግረወዋል፡፡
መንገዱ የተዘጋውም በግጭት ምክንያት ሳይሆን እንዳልቀረ ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡ ወደ አሰብ አስክሬን ጭኖ የሚያልፍ መኪና ማየታቸውንም አክለዋል፡፡
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ጉዳዩን ፖሊስ ገና እያጣራው ነዉ ተብሏል።
-
- Senior Member+
- Posts: 33674
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: ኦነግ በምእራብ ሃረርጌ ጥቃት አደረሰ ፣ ኦህዴድ/ኦዲፒ አጥቂን በስሙ መጥራት ፈርቷል
Please wait, video is loading...
-
- Member
- Posts: 961
- Joined: 11 Jul 2018, 12:30
Re: ኦነግ በምእራብ ሃረርጌ ጥቃት አደረሰ ፣ ኦህዴድ/ኦዲፒ አጥቂን በስሙ መጥራት ፈርቷል
Really? It was skirmish between pastoralists around Awash. Big lier. Kkkk